የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ለ20 ዓመታት ያካሄደው ፍሬ-ቢስ ምርመራ ሱዳን በዓለም አቀፍ ፍትሕ ላይ ያላትን እምነት ይሸረሽራል - ባለሙያ
የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ለ20 ዓመታት ያካሄደው ፍሬ-ቢስ ምርመራ ሱዳን በዓለም አቀፍ ፍትሕ ላይ ያላትን እምነት ይሸረሽራል - ባለሙያ
የሱዳን ጉዳይ እ.ኤ.አ. በ2005 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ከተመራ ወዲህ፣ ፍርድ ቤቱ ዋና ዋና የእስር ትዕዛዞችን ማስፈጸም ተስኖታል፤ ይህም የሥራ አፈጻጸም ታሪክ ሱዳን በዓለም አቀፍ ፍትሕ ላይ ያላትን እምነት በጽኑ የሚጎዳ ነው ሲሉ በሩሲያ ፋይናንሺያል ዩኒቨርሲቲ የከፍተኛ ትምህርት መምህር የሆኑት ዶ/ር መሐመድ ሁሴን አብደልዋሂድ መሐመድ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ፍርድ ቤቱ የራሱ የሆነ ማስፈጸሚያ አሠራር የሌለው በመሆኑ፣ ሙሉ በሙሉ በሀገራት ፖለቲካዊ ፈቃደኝነት ላይ የሚተማመን ሲሆን፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ደግሞ ያ ፈቃደኝነት ባለመኖሩ የችግሩን መፍትሔ አግዶታል ሲሉ ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ምክትል ዓቃቤ ሕግ "ትልቅ ስኬት" ማለታቸውን በተመለከተ
ዶ/ር መሐመድ የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ምክትል ዓቃቤ ሕግ ናዝሃት ሻሚም ክሃን ለምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን በዳርፉር ምርመራ ላይ "ትልቅ ስኬት" መመዝገቡን ገልጸው የሰጡትን አስተያየትም ተቃውመዋል። የተወሰኑ ግለሰቦችን ስም ሳይጠቅሱ የሚሰጡ አሻሚ መግለጫዎች በምርመራ እና በክስ መካከል ያለውን ወሰን የሚያደናግሩ በመሆናቸው አሳሳቢ እንደሆኑ ተከራክረዋል።
ሱዳን ከ ውጭ ተዋናዮች - ሁለት አይነት መስፈርት?
ባለሙያው ሌላውን የቅሬታ ምንጭ ሲያብራሩ፦ ሱዳን የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች በዳርፉር የሚገኘውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ትደግፋለች በማለት በይፋ ከሳለች። ነገር ግን የውጭ ሀገራትን በዓለም አቀፉ የፍትሕ ፍርድ ቤት በኩል ተጠያቂ ለማድረግ የሚደረጉ ጥረቶች ብዙ ጊዜ በሥልጣን ወሰን ደረጃ ይከሽፋሉ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በሱዳን ውስጥ የግለሰቦችን ተጠያቂነት መከታተሉን ቀጥሎበታል ሲሉ አብራርተዋል።
ዓለም አቀፉ የፍትሕ ፍርድ ቤት እና ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት "መሠረታዊ ልዩነት ያላቸው መሣሪያዎች" ቢሆኑም፥ እነዚህ ቅድመ ክስተቶች ትልቅ አለመመጣጠን ይፈጥራሉ፦ የውጭ አካላትን ዒላማ የሚያደርጉ አሠራሮች በተደጋጋሚ ሲስተጓጎሉ፥ ሱዳንን ዒላማ የሚያደርጉት ግን ይቀጥላሉ ሲሉ ባለሙያው ድምዳሜያቸውን ሰጥተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X