ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት በጥቅምቱ የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ማረጋገጫ ሰጡ - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

ሰብስክራይብ

ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት በጥቅምቱ የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ማረጋገጫ ሰጡ - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ዲፓርትመንት ዳይሬክተር አናቶሊ ባሽኪን ለሩሲያ መገናኛ ብዙኃን እንደተናገሩት፤ "በአፍሪካ 54 ሀገራት መኖራቸውን ስናስብ፥ ይህ በጣም ትልቅ ስኬት ነው። አሁንም ከፊታችን ጊዜ አለን፤ ሂደቱም በቀጣይነት ላይ ነው። በየቀኑ ቁጥራቸው እየጨመረ የመጣ ሀገራት በጉባኤው ላይ ለመገኘት ፍላጎታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።"

እንደ ባሽኪን ገለጻ፥ ሞስኮ የቻድ ፕሬዚዳንት ማሃማት ኢድሪስ ዴቢ ኢትኖ በጉባኤው ላይ እንደሚገኙ የሚገልጽ የጽሑፍ ማረጋገጫ በመጠባበቅ ላይ ነች። ሁለቱም ወገኖች ከጉባኤው ጎን ለጎን በፕሬዚዳንት ዴቢ እና በሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን መካከል የሁለትዮሽ ስብሰባ ለማዘጋጀት ፍላጎት እንዳላቸውም አክለዋል።

በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ ማረጋገጫ የሰጡ ሀገራት መካከል፦ ማሊ፣ ማደጋስካር፣ ኡጋንዳ፣ ኬንያ፣ ግብፅ፣ ጊኒ-ቢሳውቡሩንዲ እና ሱዳን ይገኙበታል።

ሦስተኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ጥቅምት 18 እና 19 በሞስኮ ይካሄዳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0