በሥልጣን ላይ ያሉት የሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ ፕሬዚዳንት ለሁለተኛ የሥራ ዘመን በድጋሚ ተመርጠዋል - ጊዜያዊ ውጤት

ሰብስክራይብ

በሥልጣን ላይ ያሉት የሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ ፕሬዚዳንት ለሁለተኛ የሥራ ዘመን በድጋሚ ተመርጠዋል - ጊዜያዊ ውጤት

ፕሬዚዳንት ካርሎስ ቪላ ኖቫ ለተጨማሪ አምስት ዓመታት በሥልጣን ላይ ለመቆየት የተቃረቡ ሲሆን፤ የሀገሪቱ ብሔራዊ ምርጫ ኮሚሽን ያወጣውን ጊዜያዊ ውጤት የጠቀሱ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት 55.94 በመቶ ድምጽ አግኝተዋል

በምርጫው ዋና ተቀናቃኛቸው የነበሩት ኒቶ ዲአብሬው 41.42 በመቶ ድምጽ ያገኙ ሲሆን፣ ሌሎቹ ሁለቱ ዕጩዎች ዩጄኒዮ ቲኒ እና ሚኬስ ጆአዎ ማግኘት የቻሉት 1.97 በመቶ እና 1.58 በመቶ ድምጽ ብቻ መሆኑን መገናኛ ብዙኃን ገልጸዋል።

እሁድ ዕለት በተደረገው ምርጫ ከ142,000 በላይ ዜጎች ድምጽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቅ የነበረ ቢሆንም፤ የምርጫው ዕለት ዝቅተኛ የሕዝብ ተሳትፎ የታየበት እንደነበር ምርጫ ኮሚሽኑ አስታውቋል።

ፕሬዚዳንት ቪላ ኖቫ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ላይ ድምጻቸውን ሲሰጡ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0