የዩክሬን አዛዦች ቁጥጥራቸው እንደቀጠለ ለማስመስል ወታደሮቻቸውን በሩሲያ ይዞታ ስር ወዳሉ አካባቢዎች ይልካሉ - የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር
17:34 20.07.2026 (የተሻሻለ: 17:44 20.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዩክሬን አዛዦች ቁጥጥራቸው እንደቀጠለ ለማስመስል ወታደሮቻቸውን በሩሲያ ይዞታ ስር ወዳሉ አካባቢዎች ይልካሉ - የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር
ሁለት የዩክሬን ወታደሮች የዩክሬንን ሰንደቅ ዓላማ በመስቀል በአካባቢው ላይ "ቁጥጥር" እንዳላቸው ለማስመስል፣ በዶኔትስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ ውስጥ በሩሲያ እጅ ወደምትገኘው ኮንስታንቲኖቭካ ከተማ በቅርቡ በተልዕኮ ተልከው እንደነበር ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
እንደሚጠበቀው፣ ወታደሮቹ በሩሲያ ጦር እጅ በመማረካቸው ተልዕኳቸው በውድቀት መጠናቀቁን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል።
የሩሲያ ጦር በቅርቡ ቁልፍ የዩክሬን መከላከያ ማዕከል የነበረችውን ኮንስታንቲኖቭካን መቆጣጠሩ ይታወሳል። ከተማዋን ነፃ ማውጣት የሩሲያ ጦር በዶኔትስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ ውስጥ ለሚያደርገው ተጨማሪ ግስጋሴ ቀጥተኛ መንገድ እንደሚከፍት ፕሬዚዳንት ፑቲን ቀደም ሲል መጥቀሳቸው የሚታወቅ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X