አፍሪካ በተጨባጭ የአኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነቱ የሚጠበቁትን ጥቅሞች እውን እንዲያደርግ መሥራት አለባት - ኢትዮጵያዊ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

አፍሪካ በተጨባጭ የአኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነቱ የሚጠበቁትን ጥቅሞች እውን እንዲያደርግ መሥራት አለባት - ኢትዮጵያዊ ባለሙያ

የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን አነስተኛ የንግድ ልውውጥ ክፍተት ለማጥበብ አንድ እርምጃ ወደፊት የተራመደ መሆኑን የምጣኔ ሃብት ባለሙያው ዶ/ር አሰፋ አድማሴ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

"ተጨባጭ እርምጃዎች ያስፈልገናል፡፡  በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን ትስስር ማሻሻል ያስፈልገናል፡፡ ይህ ትስስር ደግሞ የዲጂታል ትስስር መሆን አለበት። በመንገድ ትስስር ረገድ መሆን አለበት፤ በኃይል ትስስር ረገድ መሆን አለበት፡፡ እነዚህ ሁሉ በአፍሪካ ሀገራት ውስጥ እና በመካከላቸው ንግድን ለማሳደግ ወሳኝ ግብዓቶች ናቸው።" ብለዋል፡፡

ባለሙያው፣ ከ23ኛው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማኅበር ኮንፈረንስ ጎን ለጎን ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ባደረጉት  ቆይታ ያነሷቸውን ተጨማሪ ሐሳቦች ለማወቅ ቪዲዮውን ይመልከቱ፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0