ሱዳን አዲሱን የአሜሪካ ማዕቀብ «የአንድ ወገን እና ሕገ-ወጥ» ነው በማለት ውድቅ አደረገች
13:45 20.07.2026 (የተሻሻለ: 15:24 20.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሱዳን አዲሱን የአሜሪካ ማዕቀብ «የአንድ ወገን እና ሕገ-ወጥ» ነው በማለት ውድቅ አደረገች
ከሰኞ ጀምሮ ተግባራዊ የሆነው ይህ ማዕቀብ የተጣለው፥ ዋሽንግተን የሱዳን መከላከያ ኃይል ከኬሚካል እና ባዮሎጂካል መሣሪያዎች ቁጥጥር ጋር የተያያዙ ግዴታዎችን አልተወጣም ብላ ከከሰሰች በኋላ ነው። የተወሰዱት እርምጃዎች ዓለም አቀፍ ተቋማዊ ብድሮችን የማግኘት ዕድልን የሚገድቡ፣ አብዛኞቹን የአሜሪካ ወጪ ምርቶች ወደ ሱዳን እንዳይገቡ የሚከለክሉ እና የቴክኖሎጂ ኤክስፖርትን የሚያግዱ ናቸው።
የሱዳን ምላሽ
አሜሪካ በኬሚካዊ መሣሪያዎች ስምምነት መሠረት የተቀመጡትን የአሠራር ሂደቶች በመተላለፍ፥ መሠረተ ቢስ በሆኑ ክሶች ላይ ተመስርታለች ሲል የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ሱዳን የኬሚካል መሣሪያዎችን አታመርትም፣ አትታጠቅም አልያም አትጠቀምም ሲል በድጋሚ ያረጋገጠ ሲሆን፤ ማዕቀቡ ታማኝ በሆነ ማስረጃ ላይ ከተመሠረተ ይልቅ ፖለቲካዊ ዓላማ ያነገበ ነው በማለት ሞግቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X