የሱዳኑ አል-ቡርሃን የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር ኤርትራን ጎበኙ፤ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋርም ተወያዩ

ሰብስክራይብ

የሱዳኑ አል-ቡርሃን የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር ኤርትራን ጎበኙ፤ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋርም ተወያዩ

ጉብኝቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው የሁለትዮሽ ግንኙነት እና በተለያዩ ዘርፎች ትብብርን ማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ያተኮረ መሆኑን የሱዳን ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት በመግለጫው አስታውቋል።

ቁልፍ ዝርዝሮች፦

መሪዎቹ በካርቱም እና በአሥመራ መካከል ስላለው ግንኙነት የተወያዩ ሲሆን፤ "በሁለቱ ሕዝቦች መካከል ያለውን የወንድማማችነት ትስስር" ይበልጥ ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑ ላይ ተስማምተዋል።

ጉብኝቱ ሁለቱ ሀገራት በክልላዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ቅንጅት እንዲሁም በቀጣናው ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚደረጉ ጥረቶችን የሚያንጸባርቅ ነው።

"ጉብኝቱ በሁለቱ ሀገራት ሕዝቦች መካከል ያለውን ጥልቅ ወንድማማችነት እና ፍቅር የሚገልጽ ነው" ሲል ጽሕፈት ቤቱ አስታውቋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
የሱዳኑ አል-ቡርሃን የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር ኤርትራን ጎበኙ፤ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋርም ተወያዩ - Sputnik አፍሪካ
1/3
© telegram sputnik_ethiopia
የሱዳኑ አል-ቡርሃን የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር ኤርትራን ጎበኙ፤ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋርም ተወያዩ - Sputnik አፍሪካ
2/3
© telegram sputnik_ethiopia
የሱዳኑ አል-ቡርሃን የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር ኤርትራን ጎበኙ፤ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋርም ተወያዩ - Sputnik አፍሪካ
3/3
1/3
2/3
3/3
አዳዲስ ዜናዎች
0