በትንሽ መጠን የሚደረጉ ቅናሾች እንኳ ሰፊ ውጤት አላቸው - ባለሙያ በኬንያ የነዳጅ ድጎማ ላይ

ሰብስክራይብ

በትንሽ መጠን የሚደረጉ ቅናሾች እንኳ ሰፊ ውጤት አላቸው - ባለሙያ በኬንያ የነዳጅ ድጎማ ላይ

የ7.3 ሚሊዮን ዶላር የነዳጅ ድጎማው አነስተኛ ሊመስል ቢችልም፥ በማደያዎች በሚሸጠው ነዳጅ ላይ የሚደረጉ አነስተኛ ቅናሾች እንኳ የትራንስፖርት እና የማምረቻ ወጪዎችን ለመቀነስ ያግዛሉ ሲሉ የልማት ኢኮኖሚስት ዋንያማ ዋንጃላ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

«እዚህ የምትቆጥቧት አምስት ሺሊንግ፥ ሌላ ቦታ የሚገኝ ሌላ ሰው 50 ሺሊንግ እንዲቆጥብ ለማድረግ ትበቃለች፤ ይህም በቀኑ መገባደጃ ላይ ለአንድ ሰው የዕለት ምግብ መግዣ ይሆናል» ሲሉ ተናግረዋል።

የኢኮኖሚስቱ ቁልፍ ነጥቦች፦

🟠ዓለም አቀፋዊ ችግር፦ የኬንያ የነዳጅ ዋጋ ተግዳሮቶች ከሀገሪቱ ቁጥጥር ውጭ በሆኑ ዓለም አቀፍ ክስተቶች ሳቢያ የመጡ ናቸው፤ ከእነዚህም መካከል ወረርሽኙ፣ የሩሲያ-ዩክሬን ግጭት እና በቅርቡ ከኢራን ጋር በተያያዘ የተከሰቱት ውጥረቶች ይገኙበታል።

🟠የመንግሥት ለመንግሥት ስምምነት፦ የተደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት መካከለኛ ነጋዴዎች ላይ ያለውን ጥገኝነት በመቀነስ፣ ዋጋን በማረጋጋት እና በዓለም አቀፍ አለመረጋጋት ወቅት እንኳ ያልተቋረጠ አቅርቦት እንዲኖር በማድረግ የነዳጅ ዋስትናን አጠናክሯል።

🟠ዘላቂነት፦ ምንም እንኳ የነዳጅ ድጎማዎች በረጅም ጊዜ የፋይናንስ ዘላቂነት ባይኖራቸውም፣ ሸማቾችን ከዓለም አቀፍ ድንገተኛ የዋጋ ግሽበት ለመታደግ እንደ ጠቃሚ የአጭር ጊዜ መሣሪያ ያገለግላሉ።

ለተጨማሪ ዝርዝር መረጃ የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ ያዘጋጀውን ሙሉ ዘገባ ይመልከቱ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0