🪖 የሩሲያ ጦር በዩክሬን ግጭት በሁሉም ግንባሮች እየገሰገሰ ነው — የሩሲያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም
🪖 የሩሲያ ጦር በዩክሬን ግጭት በሁሉም ግንባሮች እየገሰገሰ ነው — የሩሲያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም
የሩሲያ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ቫለሪ ጌራሲሞቭ የ "ዛፓድ" (ምዕራብ) ጦር ስብስብን በጎበኙበት ወቅት ስለ ጦር ሜዳው ወቅታዊ ሁኔታ ሪፖርቶች ደርሷቸዋል።
ዋና ዋና መግለጫዎች፦
🟠 የ "ዛፓድ" ጦር ስብስብ የዩክሬን ኃይሎች ወደ ምዕራባዊው የኩፒያንስክ ክፍል ለመግባት እና የሩሲያን ጦር ወደ ኦስኮል ወንዝ ምስራቃዊ ዳርቻ ለመግፋት ያደረጉትን ሙከራ መክቷል።
🟠 የሩሲያ ወታደሮች የክራስኒ ሊማንን ነፃ የማውጣት ሂደት እያጠናቀቁ ሲሆን በከተማዋ የነበረው የተቀናጀ የዩክሬን መከላከያ ተሰብሯል።
🟠 የ "ዩግ" የጦር ስብስብ ኮንስታንቲኖቭካን ነፃ ካወጣ በኋላ ወደ ድሩዥኮቭካ እየገሰገሰ ሲሆን የፊት መስመር ክፍሎች ወደ አሌክሴቮ-ድሩዥኮቭካ ገብተዋል።
🟠 ወደ ስላቭያንስክ እና ክራማቶርስክ እየገሰገሱ ያሉ የሩሲያ ኃይሎች ፒስኩኖቭካን ነፃ ያወጡ ሲሆን ወደ ኒኮላዬቭካ ዳርቻዎች ደርሰዋል።
🟠 ወታደሮቹ አሁን ከክራማቶርስክ ምስራቃዊ ዳርቻ በ5 ኪሎ ሜትር ባነሰ ርቀት ላይ ይገኛሉ።
🟠 የ "ትሴንትር" ጦር ስብስብ ከክራስኖአርሜይስክ በስተሰሜን ጥቃቱን እያሰፋ ሲሆን በዶብሮፖልዬ እና በአንኖቭካ ውጊያ ቀጥሏል።
🟠 የሌኒና መንደር በሩሲያ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን የሼቭቼንኮ፣ ክራስኖያርስኪ እና ስቬትሊን ነፃ የማውጣት ሂደት ተቃርቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X