ታሪክን የኋሊት፦ የአፍሪካን ወዳጆች የመምረጥ መብት የአፍሪካውያን ነው - የማንዴላ ዘመን ተሻጋሪ ትምህርት
17:18 18.07.2026 (የተሻሻለ: 17:24 18.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ታሪክን የኋሊት፦ የአፍሪካን ወዳጆች የመምረጥ መብት የአፍሪካውያን ነው - የማንዴላ ዘመን ተሻጋሪ ትምህርት
በዓለም አቀፉ የኔልሰን ማንዴላ ቀን ስፑትኒክ አፍሪካ እ.አ.አ በሰኔ 1990 ማንዴላ ከእስር ከተፈቱ በኋላ ወደ አሜሪካ ባደረጉት ጉብኝት ወቅት የተደረገውን የማይረሳ ቃለ ምልልስ በድጋሚ ይቃኛል።
በኒውዮርክ በተካሄደ የኤቢሲ ኒውስ የሕዝብ መድረክ፤ አንድ አሜሪካዊ ቃለመጠይቅ አድራጊ በምዕራባውያን ዘንድ እንደ ጠላት ከሚታዩ መሪዎች ጋር ስላላቸው ግንኙነት ማንዴላን ሞግቷቸው ነበር። ማንዴላም በእርጋታ ጊዜ የማይሽረው ምላሽ ሰጥተዋል።
"አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ከሚሰሯቸው ስህተቶች አንዱ የእነርሱ ጠላቶች የእኛም ጠላቶች መሆን አለባቸው ብለው ማሰባቸው ነው።"
ማንዴላ ድምፃቸውን ከፍ ሳያደርጉ ወይም ለተወረወረላቸው ማጥመጃ ሳይጋለጡ አንድ ቀላል መርህን በድጋሚ አረጋግጠዋል። የአፍሪካን አጋሮች የሚመርጡት ራሳቸው አፍሪካውያን ብቻ ናቸው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X