የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎች ያስተዋወቀ የኢትዮጵያ-ሩሲያ ቢዝነስ ፎረም በሞስኮ ተካሄደ

ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት ዕድሎች ያስተዋወቀ የኢትዮጵያ-ሩሲያ ቢዝነስ ፎረም በሞስኮ ተካሄደ

 

መድረኩ የሁለቱን ሀገራት የንግድ ግንኙነት የማጠናከር ዓላማ አንግቦ እንደተካሄደ በሩሲያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

 

የሞስኮ ኤክስፖርት ማዕከል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቪታሊ ስቴፓኖቭ እና በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ልውውጥ ለማሳደግ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ እንደሆኑ አፅንኦት ሰጥተዋል።

 

የሁለቱ ሀገራት ተቋማት ተወካዮች የሞስኮን የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት፣ የኢትዮጵያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲሁም የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ለማሳደግ የሚደረጉ ድጋፎችን ጨምሮ ስላሉት አመቺ ሁኔታዎች በዝርዝር አቅርበዋል።

 

በሩሲያ የንግድ ተቋማት እና በኢትዮጵያ የስራ ሃላፊዎች መካከል ከተካሄደው ቀጥተኛ የጥያቄ እና መልስ መርሃ ግብር በመቀጠል፤ ሁለቱም ወገኖች በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ቴክኖሎጂ እና ከፍተኛ ትምህርት ዘርፎች ትብብራቸውን ለማስፋት ተስማምተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0