ሊቢያ ኢኮኖሚዋን እና ቀጣናዊ መረጋጋትን ለማሳደግ የሩሲያን ኢንቨስትመንት ትሻለች - ሚኒስትር
14:32 18.07.2026 (የተሻሻለ: 16:34 18.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሊቢያ ኢኮኖሚዋን እና ቀጣናዊ መረጋጋትን ለማሳደግ የሩሲያን ኢንቨስትመንት ትሻለች - ሚኒስትር
ሊቢያ በሀገሪቱ እና በጎረቤት የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ልማት ላይ አስተዋጽዖ ሊያበረክቱ የሚችሉ የጋራ ፕሮጀክቶችን ለመተግበር ምልከታ እያደረገች መሆኑን የሊቢያ ፓርላማ ተሿሚ መንግሥት የአፍሪካ ጉዳዮች ባለሙሉ ሥልጣን ሚኒስትር ኢሳ አብደልመጂድ መንሱር ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
ከሚኒስትሩ ንግግሮች የተገኙ ዋና ዋና ነጥቦች፦
◻ ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንቶች በትምህርት፣ በጤና፣ በትራንስፖርት፣ በመንገዶች እና በሌሎች ዘላቂ የልማት ዘርፎች ላይ ማተኮር አለባቸው።
◻ የሊቢያ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ እና ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላት ታሪካዊ ትስስር የውጭ ባለሀብቶችን ከአኀጉራዊ ገበያዎች ጋር የሚያገናኝ "የአፍሪካ መግቢያ በር" ያደርጋታል።
◻ የጎረቤት ሀገራትን ኢኮኖሚ ማልማት የሥራ እድልን ይፈጥራል፣ የስደት ስጋቶችን ይቀንሳል እንዲሁም የድንበር ደህንነትን ያጠናክራል፤ ይህም በሳኀል ቀጣና እና ባሻገር ዘላቂ መረጋጋትን ይደግፋል።
"ሩሲያ፣ ቻይና ወይም በአፍሪካ ኢንቨስት ለማድረግ እና የልማት ፕሮጀክቶችን ለመተግበር የምትፈልግ ሌላ ሀገር የራሷን ጥቅም የመፈለግ መብት አላት። ሊቢያ ጥቅሟን ለማስጠበቅ እና ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ ናት።"
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X