የዲአርሲ መንግሥት እና ኤም23 በጎማ የጋራ የተኩስ አቁም ክትትል ሥርዓት አዋቀሩ
08:31 18.07.2026 (የተሻሻለ: 08:34 18.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዲአርሲ መንግሥት እና ኤም23 በጎማ የጋራ የተኩስ አቁም ክትትል ሥርዓት አዋቀሩ
ኤም23ን በሚያካትተው የኮንጎ ወንዝ አማፂያን ጥምረት እና በኮንጎ
ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል በተደረሰው የተኩስ አቁም መከታተያ ሥርዓት፤ ሦስት የዲአርሲ ጦር ኃይል መኮንኖች ጎማ ከተማ መድረሳቸውን ተከትሎ ሙሉ በሙሉ ሥራ መጀመሩን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ዋና ዋና ዝርዝሮች፦
ይህ ሥርዓት የተኩስ አቁም ስምምነቱ መከበሩን የመከታተል፣ ጥሰቶችን የመመርመር እና ዳግም ወደ ግጭት እንዳይመለስ የማገዝ ኃላፊነት አለበት።
የዲአርሲ መንግሥት፣ የኮንጎ ወንዝ አማፂያን ጥምረት/ኤም23፣ የታላላቅ ሐይቆች ቀጣና ዓለም አቀፍ ጉባኤ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ተልዕኮ (ሞኑስኮ) ተወካዮችን ያካተተ ሲሆን የአፍሪካ ኅብረት፣ ኳታር እና አሜሪካ በታዛቢነት ይሳተፋሉ።
የተኩስ አቁም ክትትል ስምምነቱ የተፈረመው እ.አ.አ 2025 በዶሃ በተካሄደውና በኳታር አደራዳሪነት በተከናወነው የሰላም ንግግር ወቅት ነበር። ወገኖቹ በየካቲት ወር በአሠራር ሂደቶች ዙሪያ የተስማሙ ሲሆን በሚያዝያ ደግሞ የዕቅድ ትግበራውን ጀምረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X