ናሚቢያ በጋራ የንግድ ምክር ቤት አማካኝነት ከደቡብ አፍሪካ ጋር የኢንዱስትሪ ትስስሯን ማጠናከር እንደምትፈልግ የንግድ ሚኒስትሯ ገለጹ
16:08 17.07.2026 (የተሻሻለ: 16:14 17.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ናሚቢያ በጋራ የንግድ ምክር ቤት አማካኝነት ከደቡብ አፍሪካ ጋር የኢንዱስትሪ ትስስሯን ማጠናከር እንደምትፈልግ የንግድ ሚኒስትሯ ገለጹ
ናሚቢያ እና ደቡብ አፍሪካ ለቀጣናው መረጋጋት እጅግ ወሳኝ የሆነና የተሳሰረ የኢንዱስትሪ ሥነ-ምህዳር እንደሚጋሩ የናሚቢያ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ንግድ ሚኒስትር ሴልማ አሺፓላ-ሙሳቪዪ በፕሪቶሪያ በተካሄደው አራተኛው የሁለትዮሽ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ልውውጥ አሁንም ሚዛናዊ አይደለም። እ.ኤ.አ በ2025 የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ መጠኑ 5.3 ቢሊዮን ዶላር የደረሰ ሲሆን ናሚቢያ 1.8 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ጥሬ ዕቃዎችን (ማዕድናት፣ ዓሣ እና የቤት እንስሳት) ስትልክ፤ በምላሹ እንደ ተሽከርካሪዎች እና ማሽነሪዎች ያሉ 3.5 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው የተመረቱ ምርቶችን ከደቡብ አፍሪካ እንዳስገባች ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
ይህንን የንግድ ጉድለት ለመሙላት እና የናሚቢያን የኢንዱስትሪ መሠረት ለማስፋፋት፤ የግል ኢንቨስትመንት፣ የጋራ የንግድ ሽርክናዎች እና ውጤታማ አጋርነቶችን የሚያበረታታ "የደቡብ አፍሪካ-ናሚቢያ የንግድ ምክር ቤት" በአስቸኳይ እንዲቋቋም አሺፓላ-ሙሳቪዪ ጥሪ አቅርበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X