ኢትዮጵያ በአብዛኛው የታሪክ ዘመኗ የባሕር በር የሌላት አልነበረችም - ሊቢያዊ ፕሮፌሰር

© telegram sputnik_ethiopiaኢትዮጵያ በአብዛኛው የታሪክ ዘመኗ የባሕር በር የሌላት አልነበረችም - ሊቢያዊ ፕሮፌሰር
ኢትዮጵያ በአብዛኛው የታሪክ ዘመኗ የባሕር በር የሌላት አልነበረችም - ሊቢያዊ ፕሮፌሰር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 17.07.2026
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ በአብዛኛው የታሪክ ዘመኗ የባሕር በር የሌላት አልነበረችም - ሊቢያዊ ፕሮፌሰር

የሀገሪቱ የባሕር በር ፍላጎትም የሕግ መርሆዎችን፣ ዓለም አቀፍ ሕግ እና ክልላዊ ስምምነቶችን መሠረት ያደረገ ነው ሲሉ ፕሮፌሰር ሳድ ሳላማ ለፐልስ ኦፍ አፍሪካ በሰጡት ቃለምልልስ ተናግረዋል።

"ሁሉም ዓለም አቀፍ ሕጎች እና ቀጣናዊ የሕግ ማዕቀፎች የባሕር በር ለሌላቸው ሀገራት ወደ ባሕር የመድረስ መብት ይሰጣሉ። ይህ ሕጋዊ የሆነ ጥያቄ ነው፤ ዓለም አቀፍ ሕግም የባሕር በር ለሌላቸው ሀገራት የባሕር መውጫ የማግኘት መብታቸውን ያረጋግጣል” ሲሉ ለሚዲያው አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ እና ለቀይ ባሕር ያላት ቅርበትም የሁሉንም ወገኖች ጥቅም የሚያስከብሩ የትብብር መፍትሔዎችን ለመፈለግ የምታቀርበውን አመክንዮ ያጠናክራል ብለዋል።

“ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት ከጎረቤት ሀገራት ወይም የባሕር ጠረፍ ካላቸው ሀገራት የሚሰጥ ስጦታ ወይም ችሮታ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባም። ይህ በሁሉም ዓለም አቀፍ የሕግ ሰነዶች የተረጋገጠ ተፈጥሯዊ መብት ነው” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0