ድንበር አልባ ደቡብ አፍሪካን ለመፍጠር የቅኝ አገዛዝ መሠረተ ልማቶች መፈራረስ አለባቸው - የኤኤንሲ የወጣቶች ሊግ መሪ
15:04 17.07.2026 (የተሻሻለ: 15:14 17.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ድንበር አልባ ደቡብ አፍሪካን ለመፍጠር የቅኝ አገዛዝ መሠረተ ልማቶች መፈራረስ አለባቸው - የኤኤንሲ የወጣቶች ሊግ መሪ
"የአፍሪካ ድህነት፤ ምንም ዓይነት የማዕድን ሀብት የሌላቸው አካላት ከሀብቷ ያለማቋረጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ነው" ሲሉ የደቡብ አፍሪካ ገዢ ፓርቲ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ የወጣቶች ሊግ ፕሬዝዳንት ኮለን ማላትጂ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ማላትጂ ለተባበረች አፍሪካ ወሳኝ ናቸው ያሏቸው ዋና ዋና እርምጃዎች የሚከተሉት ናቸው፦
▪ ከቅኝ አገዛዝ ኢኮኖሚያዊ መዋቅሮች ነፃ ለመውጣት የሚያስችል የጋራ የአፍሪካ መገበያያ ገንዘብ መተግበር፣
▪ በቅኝ ግዛት ቋንቋዎች የመጡ ክፍፍሎችን በማሸነፍ የጋራ የንግድ መግባቢያ ቋንቋ መመስረት፣
▪ የቀድሞ ቅኝ ገዥዎች የአፍሪካን የማዕድን ሀብት መበዝበዛቸውን በሚቀጥሉበት በኒዮ-ኮሎኒያሊዝም አስተሳሰብ ላይ በጋራ መቆም።
"በዓለም እጅግ ባለጸጋ ሀገር መሆን የሚገባትን ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክን ብንመለከት፤ ባላት ከፍተኛ የማዕድን ክምችት ምክንያት እየተሰቃየች ትገኛለች። ቅኝ ገዥዎች አሁንም የዚያችን ሀገር ሕዝብና ማዕድናት እየበዘበዙ ይገኛሉ።"
የድንበር ቁጥጥር እና የሠራተኞች ክትትል ሕጋዊ ስደተኞችንም ሆነ የሀገር ውስጥ ሠራተኞችን እንዴት እንደሚጠብቁ ለመገንዘብ ቪዲዮውን ይመልከቱ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X