የምዕራቡ ዓለም ሀገራት የኤአይ ቴክኖሎጂዎችን ለጠላታዊ ዓላማዎች እየተጠቀሙባቸው ነው - የሩሲያ ባለሥልጣን
የምዕራቡ ዓለም ሀገራት የኤአይ ቴክኖሎጂዎችን ለጠላታዊ ዓላማዎች እየተጠቀሙባቸው ነው - የሩሲያ ባለሥልጣን
በሻንጋይ ከተከፈተው የዓለም የሰው ሠራሽ ኮንፈረንስ ጎን ለጎን የፕሬዚዳንት አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ማክስም ኦሬሽኪን የሰጧቸው ሌሎች መግለጫዎች፦
▪ አዲስ የተቋቋመው የዓለም የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ትብብር ድርጅት (ዊኮ) የሰው ሠራሽ አስተውህሎትን (ኤአይ) በመቆጣጠር ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል፣
▪ ከሁሉም የዊኮ መስራች ሀገራት ቻይና እና ሩሲያ በኤአይ ልማት ረገድ የላቀ ስኬት አስመዝግበዋል፣
▪ ሩሲያ እና ቻይና በሻንጋይ በነበራቸው ቆይታ በኤአይ ትብብር ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን በኩባንያዎቻቸው መካከል ያለው አጋርነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ይሸጋገራል፣
▪ ሩሲያ የራሷን የኤአይ መፍትሄዎች ለአጋር ሀገራት የምታቀርብ ሲሆን እነዚህም በዓለም ዙሪያ በሚገኙ በደርዘን የሚቆጠሩ ሀገራት ውስጥ ተግባር ላይ እየዋሉ ይገኛሉ፣
▪ ሩሲያ በኤአይ ሳቢያ የሚደቀኑ ስጋቶችን በመከላከል ረገድ ሰፊ ልምድ አላት፣
▪ ሩሲያ የኤአይ ቴክኖሎጂዎችን በኢኮኖሚው ውስጥ በመተግበር ረገድ ከዓለም መሪ ሀገራት አንዷ ነች፣
▪ አሜሪካ የኤአይ ቴክኖሎጂዎችን ለሌሎች የማታጋራው በቴክኖሎጂው ሌሎችን ለመበዝበዝ በማሰብ ነው። በአንጻሩ የሩሲያ እና የቻይና ኤአይ ሞዴሎች ለሁሉም ተደራሽ ናቸው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X