ባሕላዊ ዲፕሎማሲ በሕዝቦች የጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ ፍትሐዊና ባለ ብዙ-ዋልታ ዓለምን ለመቅረጽ ወሳኝ መሣሪያ ነው - አምባሳደር ይቭጌኒ ተረኺን

ሰብስክራይብ

ባሕላዊ ዲፕሎማሲ በሕዝቦች የጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ ፍትሐዊና ባለ ብዙ-ዋልታ ዓለምን ለመቅረጽ ወሳኝ መሣሪያ ነው - አምባሳደር ይቭጌኒ ተረኺን

በታላቁ የሩሲያ የሙዚቃ አቀናባሪ ፒዮትር ኢሊች ቻይኮቭስኪ የተሰየመ እና የሞስኮ ስቴት ኮንሰርቫቶሪ የሙዚቃ ተማሪዎች የሩሲያን እና ዓለም አቀፍ የክላሲካል ስራዎችን ያቀረቡበት የሙዚቃ ድግስ በዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ተካሂዷል።

ዝግጅቱን በንግግር የከፈቱት በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ይቭጌኒ ቸረኺን፤ “ኪነ-ጥበብን በሰው ሰራሽ መንገድ በፖለቲካ ለመበከል እና ‘የማግለል ባሕል’ ለመጫን የሚደረጉ አጥፊ ሙከራዎችን በምናይበት በዚህ ዘመን፤ የሩሲያ ፌዴሬሽን ወጥ የሆነና ዓለም አቀፋዊ የባሕል ቅርስ እንዲቀርብ፣ የሰብዓዊ ግንኙነቶች ከፖለቲካ እንዲጸዱ እንዲሁም ክፍትና ፍትሐዊ ውይይት እንዲኖር በቋሚነት ትሟገታለች” ብለዋል።

አምባሳደሩ የሩሲያ የትምህርት ተቋማት ካላቸው ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ክብር አንጻር እንዲህ ያሉ ጉብኝቶች ሩሲያ ውስጥ ልዩ ትምህርት ለማግኘት ለሚፈልጉ ጎበዝ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች አዳዲስ ዕድሎችን እንደሚከፍቱም ገልጸዋል።

በሙዚቃ ኮንሰርቱ ላይ የመንግሥት ተወካዮች፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ የሙዚቃ ባለሙያዎች እና በአዲስ አበባ የሚገኙ የሩሲያ ማሕበረሰብ አባላት ተገኝተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0