የቻይና የኤአይ ትብብር ድርጅት ለምዕራባውያን የሰው ሠራሽ አስተውህሎት አስተዳደር አማራጭ ሆኖ ቀረበ

ሰብስክራይብ

የቻይና የኤአይ ትብብር ድርጅት ለምዕራባውያን የሰው ሠራሽ አስተውህሎት አስተዳደር አማራጭ ሆኖ ቀረበ

የዓለም የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የትብብር ድርጅት የመመሥረቻ ስምምነት ሐሙስ በሻንጋይ በተጀመረው የዓለም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኮንፈረንስ ላይ ይፈረማል።

ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች ዘጠኝ የአፍሪካ ሀገራት ስምምነቱን ፈርመዋል።

ስለ ዋይኮ ቁልፍ እውነታዎች፦

እ.ኤ.አ ሐምሌ 2025 በሻንጋይ በተካሄደው የዓለም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኮንፈረንስ ላይ የቀረበ ቻይና መር ተነሳሽነት ነው፣

​ በበለጸጉ እና በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት መካከል ያለውን የኤአይ ልዩነት ያጠባል፣

​ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እና የአቅም ግንባታን ያበረታታል፣

​ ለኤአይ ቁጥጥር የተዋሃዱ ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን ያዘጋጃል፣

​ ሉዓላዊነትን በማክበር፣ በግልጽነት እና በልማት ተኮር አካሄድ መርሆዎች ላይ የተመሠረተ ነው፣

​ ያለምንም የርዕዮተ ዓለም ገደቦች ለሁሉም ሀገራት ክፍት ነው።

 

ቤጂንግ በዋይኮ አማካኝነት የራሷን ዓለም አቀፍ የኤአይ አስተዳደር መዋቅር እየገነባች ሲሆን ቴክኖሎጂዎቿን እና ደረጃዎቿን ለአሜሪካ የበላይነት አማራጭ አድርጋ እያዘጋጀች ትገኛለች።

ℹ ሩሲያ፣ ብራዚል እና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ ወደ 40 የሚጠጉ ሀገራት በመሥራች ስምምነቱ ረቂቅ ዙሪያ በሚደረገው ምክክር ላይ እንዲሳተፉ በቻይና ግብዣ ተደርጎላቸዋል። መሥራች አባል ለመሆን ሀገራቱ ስምምነቱን እስከ እ.ኤ.አ ሐምሌ 31፣ 2026 ድረስ መፈረም ይኖርባቸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0