ናይጄሪያ በኢኮኖሚ ማሻሻያ ማዕቀፍ የሠራተኛ አስተዳደሯን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማደረግ መወጠኗ ተገለጸ

© telegram sputnik_ethiopiaናይጄሪያ በኢኮኖሚ ማሻሻያ ማዕቀፍ የሠራተኛ አስተዳደሯን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማደረግ መወጠኗ ተገለጸ
ናይጄሪያ በኢኮኖሚ ማሻሻያ ማዕቀፍ የሠራተኛ አስተዳደሯን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማደረግ መወጠኗ ተገለጸ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 16.07.2026
ሰብስክራይብ

ናይጄሪያ በኢኮኖሚ ማሻሻያ ማዕቀፍ የሠራተኛ አስተዳደሯን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማደረግ መወጠኗ ተገለጸ

​ የሀገሪቱ የሥራ እና ሠራተኛ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሐመዱ ዲንጊያዲ፤ የመንግሥትን የሠራተኛ ማሻሻያ ስኬት በከፍተኛ ደረጃ በጠንካራ የግል ዘርፍ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል።

​“ዘላቂ የሥራ ዕድል ሊገኝ የሚችለው ኢንቨስት ከሚያደርጉ፣ አዳዲስ አሠራሮችን ከሚያስተዋውቁ፣ ምርትን ከሚያስፋፉ እና ለናይጄሪያውያን ዕድሎችን ከሚፈጥሩ የንግድ ተቋማት ነው” ሲሉ መናገራቸው ተጠቅሷል።

​አክለውም፤ የሠራተኛ አስተዳደሩ ለማኅበራዊ ውይይቶች እና ለቀልጣፋ የግጭት መፍቻ ሥርዓቶች ትኩረት በመስጠት፤ ለኢኮኖሚ ዕድገት ስትራቴጂካዊ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በድጋሚ እየተቀረጸ መሆኑን ገልጸዋል።

​“...የፌዴራል መንግሥት የንግድ ሥራ ሁኔታን ለማሻሻል፣ የባለሀብቶችን እምነት ለማጠናከር እና የድርጅቶችን ዕድገት የሚያበረታቱ ፖሊሲዎችን ለማስፋፋት ቁርጠኝነቱን ይቀጥላል።”

እርምጃዎቹ የሚከተሉትን ሥርዓቶች ይበልጥ ለማሻሻል ያለሙ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፦

​▪ የሕዝብ የሥራ ስምሪት አገልግሎቶችን፣

▪ የሠራተኛ ገበያ መረጃ ሥርዓቶችን፣

▪ የሙያ ሥልጠናና ምክር አገልግሎትን።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0