የቻይና ቡና አቀነባባሪ ኩባንያ በኢትዮጵያ የተቀናጀ የቡና ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመገንባት ፍላጎት እንዳለው ገለጸ

ሰብስክራይብ

የቻይና ቡና አቀነባባሪ ኩባንያ በኢትዮጵያ የተቀናጀ የቡና ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመገንባት ፍላጎት እንዳለው ገለጸ

የሁዪቺዋን ዩንግዩ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ የቡና ማቀነባበር ዘርፍ መሰማራት በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።

በተጨማሪም ኩባንያው በቡና ዘርፍ ላይ ያለውን የኢንቨስትመንት ፍላጎት ወደ ተገባር ለመቀየር የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል።

በቻይና ሄናን ግዛት የቡና ማቀነባበሪያ ፓርክ የሚንቀሳቀሰው ይህ ኩባንያ፤ የኢትዮጵያን ቡና ለቻይና ገበያ እያቀረበ እንደሚገኝ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0