ደቡብ አፍሪካ ለእስራኤል የምታደርገው የከሰል ሽያጭ ከፕሬዚዳንቱ የአስፈፃሚ ትዕዛዝ ወሰን ውጪ ነው - የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ቃል አቀባይ

ሰብስክራይብ

ደቡብ አፍሪካ ለእስራኤል የምታደርገው የከሰል ሽያጭ ከፕሬዚዳንቱ የአስፈፃሚ ትዕዛዝ ወሰን ውጪ ነው - የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ቃል አቀባይ

​ ከንግድ አኳያ ደቡብ አፍሪካ ለእስራኤል አሰቃቂ ድርጊቶች ልትሰጥ የምትችለው ምላሽ ውስን ነው፤ ምክንያቱም አንዳንድ የደቡብ አፍሪካ እና የእስራኤል የንግድ ግንኙነቶች "በግል ኩባንያዎች መካከል በሚደረጉ ስምምነቶች" ስር የሚወድቁ በመሆናቸው ነው ሲሉ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ቃል አቀባይ ለስፑትኒክ አፍሪካ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ተናግረዋል።

ቪንሰንት ማግዌንያ፤ "ሲሪል ራማፎሳ እንዲያው በጠዋት ተነስተው ኩባንያዎች እና የንግድ ልውውጣቸው ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድር አስፈፃሚ ትዕዛዝ ለመስጠት መወሰን አይችሉም። ስለዚህ የሕግ ማዕቀፉ ምን እንደሚል መመልከት ያስፈልጋል። ከሕግ አማራጮች አንጻር ጉዳዩ ምን ይመስላል በሚለው ዙሪያ እዚሁ ቢሮአችን ውስጥ እርስ በእርሳችን የተወሰነ ክርክር አድርገናል" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0