አዲስ የፋኦ ሪፖርት የኢትዮጵያ ቡና አምራቾች በአየር ንብረት ለውጥ እና በዓለም አቀፍ የዋጋ መዋዠቅ ሳቢያ እያደገ ለመጣ ሥጋት መጋለጣቸውን ይፋ አደረገ
19:08 15.07.2026 (የተሻሻለ: 19:14 15.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አዲስ የፋኦ ሪፖርት የኢትዮጵያ ቡና አምራቾች በአየር ንብረት ለውጥ እና በዓለም አቀፍ የዋጋ መዋዠቅ ሳቢያ እያደገ ለመጣ ሥጋት መጋለጣቸውን ይፋ አደረገ
ሪፖርቱ ኢትዮጵያን ከዓለም ግንባር ቀደም የቡና ላኪ ሀገራት መካከል አንዷ አድርጎ በመጥቀስ የምርት ሂደቱ በዋናነት በሀገሪቱ ደጋማ አካባቢዎች በሚገኙ አነስተኛ ይዞታ ባላቸው አርሶ አደሮች ላይ ያተኮረ መሆኑን አመልክቷል።
የሀገሪቱ በአንድ የገቢ ሰብል ላይ ብቻ ጥገኛ መሆን ሰፊ የገጠር ኢኮኖሚዋን ለድርቅ፣ ለሙቀት መጨመር እና ለበሽታዎች መከሰት ይበልጥ ተጋላጭ እንደሚያደርገውም የጥናት ውጤቱ ገልጿል።
የፋኦ የገበያ እና ንግድ ክፍል ከፍተኛ ኢኮኖሚስት ኤል ማሙን አምሩክ፤ “አነስተኛ አምራቾች እና ገበሬዎች ያላቸውን ውሱን ሀብት እንዴት መመደብ እንዳለባቸው ትክክለኛ ውሳኔዎችን እንዲያስተላልፉ የገበያ ቅልጥፍናን እና ግልጽነትን ማሻሻል ወሳኝ ነው” ማለታቸውን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
ሪፖርቱ ገበሬዎች በሀገር ውስጥ የቡና ማቀነባበር፣ በምርት ጥራት ዕውቅና ማረጋገጫ ሥርዓቶች እና በብራንዲንግ ተግባራት ላይ እንዲሳተፉ ሰፊ ዕድሎችን በመፍጠር ከቡናው የመጨረሻ የሽያጭ ዋጋ የተሻለ ድርሻ ማግኘት እንዲችሉ ማድረግ እንደሚገባም አመልክቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X