አዲስ የፋኦ ሪፖርት የኢትዮጵያ ቡና አምራቾች በአየር ንብረት ለውጥ እና በዓለም አቀፍ የዋጋ መዋዠቅ ሳቢያ እያደገ ለመጣ ሥጋት መጋለጣቸውን ይፋ አደረገ

ሰብስክራይብ

አዲስ የፋኦ ሪፖርት የኢትዮጵያ ቡና አምራቾች በአየር ንብረት ለውጥ እና በዓለም አቀፍ የዋጋ መዋዠቅ ሳቢያ እያደገ ለመጣ ሥጋት መጋለጣቸውን ይፋ አደረገ

​ሪፖርቱ ኢትዮጵያን ከዓለም ግንባር ቀደም የቡና ላኪ ሀገራት መካከል አንዷ አድርጎ በመጥቀስ የምርት ሂደቱ በዋናነት በሀገሪቱ ደጋማ አካባቢዎች በሚገኙ አነስተኛ ይዞታ ባላቸው አርሶ አደሮች ላይ ያተኮረ መሆኑን አመልክቷል።

የሀገሪቱ በአንድ የገቢ ሰብል ላይ ብቻ ጥገኛ መሆን ሰፊ የገጠር ኢኮኖሚዋን ለድርቅ፣ ለሙቀት መጨመር እና ለበሽታዎች መከሰት ይበልጥ ተጋላጭ እንደሚያደርገውም የጥናት ውጤቱ ገልጿል።

 

የፋኦ የገበያ እና ንግድ ክፍል ከፍተኛ ኢኮኖሚስት ኤል ማሙን አምሩክ፤ “አነስተኛ አምራቾች እና ገበሬዎች ያላቸውን ውሱን ሀብት እንዴት መመደብ እንዳለባቸው ትክክለኛ ውሳኔዎችን እንዲያስተላልፉ የገበያ ቅልጥፍናን እና ግልጽነትን ማሻሻል ወሳኝ ነው” ማለታቸውን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

 

ሪፖርቱ ገበሬዎች በሀገር ውስጥ የቡና ማቀነባበር፣ በምርት ጥራት ዕውቅና ማረጋገጫ ሥርዓቶች እና በብራንዲንግ ተግባራት ላይ እንዲሳተፉ ሰፊ ዕድሎችን በመፍጠር ከቡናው የመጨረሻ የሽያጭ ዋጋ የተሻለ ድርሻ ማግኘት እንዲችሉ ማድረግ እንደሚገባም አመልክቷል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0