በቡርኪና ፋሶ እና አፍሪካ ኅብረት መካከል ያለው ግንኙነት እየተሻሻለ ነው - የቡርኪና ፋሶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
18:55 15.07.2026 (የተሻሻለ: 19:04 15.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በቡርኪና ፋሶ እና አፍሪካ ኅብረት መካከል ያለው ግንኙነት እየተሻሻለ ነው - የቡርኪና ፋሶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሐሙድ አሊ ዩሱፍ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ግንኙነት እንደገና ለማነቃቃት ባለመ የሦስት ቀን የቡርኪና ፋሶ ጉብኝታቸው ከሀገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ የሚኒስቴሩ መግለጫ አመልክቷል።
"በአኀጉራችን የሚታዩ በርካታ የጋራ ችግሮች በአጋርነት እና በአብሮነት ሊፈቱ ይችላሉ" ሲሉ አሊ ዩሱፍ ገልጸዋል።
የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የአኅጉራዊ ተቋም መሪ ከሆኑ በኋላ በሳኀል ሀገራት እያደረጉት ባለው ጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜ ቡርኪናፋ ሶን በመጎብኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን መግለጻቸውን መግለጫው ጠቅሷል።
"ቡርኪና ፋሶ የኅብረታችን አባል እና የአፍሪካ አንድነት መሥራች ሀገር ናት" ሲሉ ሊቀመንበሩ አክለዋል።
ℹ ቡርኪና ፋሶ እ.ኤ.አ በ2022 ከተደረገው የሥልጣን ለውጥ በኋላ ከአፍሪካ ኅብረት ተሳትፎ መታገዷ ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X