ናይጄሪያ በሰብዓዊ ዕርዳታ ዙሪያ በዓለም አቀፍ ለጋሾች እና በተመድ ተቋማት ላይ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ ማቀዷ ተዘገበ
18:31 15.07.2026 (የተሻሻለ: 18:34 15.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ናይጄሪያ በሰብዓዊ ዕርዳታ ዙሪያ በዓለም አቀፍ ለጋሾች እና በተመድ ተቋማት ላይ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ ማቀዷ ተዘገበ
ሀገሪቱ የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ "ኦቻ" እና ሰፊውን የተመድ መዋቅር በመጠቀም እ.ኤ.አ በ2027 የሰብዓዊ ዕርዳታ ዕቅዷን በራሷ ለመምራት መዘጋጀቷን የናይጄሪያ ሰብዓዊ ጉዳዮች ሚኒስትር በርናርድ ዶሮን ጠቅሰው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሰብዓዊ ዝግጁነት፣ ምላሽ አሰጣጥ እና መልሶ ማቋቋም ሥራዎችን ለማጠናከር ከፌዴራልና ከክልል ባለሥልጣናት፣ ከረድኤት ድርጅቶች እና ጉዳት ከደረሰባቸው ማኅበረሰቦች ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ ዶሮ ገልጸዋል።
ናይጄሪያ እና ተመድ የሰብዓዊ ዕቅድ፣ ቅንጅት እና የፋይናንስ ኃላፊነቶችን ወደ ሀገራዊ ተቋማት ይበልጥ ማቅረብ በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ በአቡጃ በተካሄደ የሽግግር አውደ ጥናት ላይ መወያየታቸው ታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X