ኢትዮጵያ ሰባት ዓይነት የህፃናት ጉሉኮስ መድኃኒቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት ጀመረች
17:16 15.07.2026 (የተሻሻለ: 17:24 15.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ሰባት ዓይነት የህፃናት ጉሉኮስ መድኃኒቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት ጀመረች
ይህም ከዚህ ቀደም መድኃኒቶቹን ከውጭ ለማስገባት ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስቀር እና በህክምናው ዘርፍ የሚታየውን የክሊኒካል አቅርቦት ክፍተት እንደሚሞላ ተነግሯል።
በተጨማሪም የመድኃኒት አቅርቦት ዋስትናን በማረጋገጥ ዓለም አቀፍ የአቅርቦት መስተጓጎል በመሠረታዊ መድኃኒቶች ላይ የሚፈጥረውን ክፈተት እንደሚሞላ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የመድኃኒት ማምረት አቅም ከሦስት ዓመታት በፊት ከነበረው 8% በአሁኑ ወቅት ወደ 44% ማደጉንም ኃላፊዋ አስታውሰዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X