የብሪክስ የግብርና ምርቶች ንግድ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ሊያጠናክር ይችላል - ባለሙያ
16:18 14.07.2026 (የተሻሻለ: 16:24 14.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የብሪክስ የግብርና ምርቶች ንግድ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ሊያጠናክር ይችላል - ባለሙያ
የብሪክስ አባል ሀገራት በየዓመቱ ወደ 300 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የምግብ ምርቶችን እንደሚያስገቡ የገለጹት የደቡብ አፍሪካ የግብርና ቢዝነስ ምክር ቤት ዋና ኢኮኖሚስት ዋንዲሌ ሲህሎቦ ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ ይህም ስብስቡን "በግብርና እና በምግብ ንግድ ረገድ እጅግ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው" ያደርገዋል ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም "በብሪክስ ስብስብ ውስጥ በግብርናው ዘርፍ እጅግ ግዙፍ አቅም ያላቸው ሀገራት አሉ" ብለዋል።
ብሪክስ የሚከተሉትን እርምጃዎች በመውሰድ የአፍሪካን የምግብ ዋስትና ሊያሻሽል ይችላል፦
🟠 የታሪፍ መጠኖችን በመቀነስ፣
🟠 የዕፅዋት ጤና ጥበቃ መሰናክሎችን በማስወገድ፣
🟠 በብሪክስ አባል ሀገራት መካከል ያለውን የርስ በርስ ንግድ ይበልጥ በማጠናከር።
"በደቡብ አፍሪካ የግብርና ዘርፍ፣ በዚሁ የብሪክስ ስብስብ ውስጥ የወጪ ንግዳችንን እና የንግድ ልውውጣችንን ይበልጥ ለማስፋት ከፍተኛ ፍላጎት አለን።"
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X