በካሜሩን ወደብ ሁለት የጭነት መርከቦች መጋጨታቸው ተገለጸ
19:24 13.07.2026 (የተሻሻለ: 19:34 13.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በካሜሩን ወደብ ሁለት የጭነት መርከቦች መጋጨታቸው ተገለጸ
የወደብ ባለሥልጣን ኃላፊዎች እንዳስታወቁት፤ ከአንደኛው መርከብ ላይ ያጋጠመ “የመሪ (የአቅጣጫ) ቁጥጥር ማጣት” እሑድ ዕለት ለተከሰተው አደጋ መንስኤ ነው ተብሎ ይታመናል።
ግጭቱ የተከሰተው አንደኛው መርከብ ከካሜሩን ዋና ዋና ወደቦች አንዱ ወደሆነው የዱአላን ወደብ እየገባ ሳለ፣ ሌላኛው ደግሞ ከወደቡ እየወጣ በነበረበት ወቅት እንደሆነ መግለጫው አስታውቋል።
አደጋው ምንም ዓይነት የሰው ሕይወት መጥፋት ወይም ጉዳት ያላስከተለ ቢሆንም፤ “በሁለቱም መርከቦች ላይ ከፍተኛ የቁስ አካል ጉዳት” ያደረሰ ሲሆን፣ በመርከቦች መተላለፊያ መስመር ላይ ያለውን የባሕር ጉዞም ለጊዜው አስተጓጉሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X