በካሜሩን ወደብ ሁለት የጭነት መርከቦች መጋጨታቸው ተገለጸ

ሰብስክራይብ

በካሜሩን ወደብ ሁለት የጭነት መርከቦች መጋጨታቸው ተገለጸ

የወደብ ባለሥልጣን ኃላፊዎች እንዳስታወቁት፤ ከአንደኛው መርከብ ላይ ያጋጠመ “የመሪ (የአቅጣጫ) ቁጥጥር ማጣት” እሑድ ዕለት ለተከሰተው አደጋ መንስኤ ነው ተብሎ ይታመናል።

ግጭቱ የተከሰተው አንደኛው መርከብ ከካሜሩን ዋና ዋና ወደቦች አንዱ ወደሆነው የዱአላን ወደብ እየገባ ሳለ፣ ሌላኛው ደግሞ ከወደቡ እየወጣ በነበረበት ወቅት እንደሆነ መግለጫው አስታውቋል።

አደጋው ምንም ዓይነት የሰው ሕይወት መጥፋት ወይም ጉዳት ያላስከተለ ቢሆንም፤ “በሁለቱም መርከቦች ላይ ከፍተኛ የቁስ አካል ጉዳት” ያደረሰ ሲሆን፣ በመርከቦች መተላለፊያ መስመር ላይ ያለውን የባሕር ጉዞም ለጊዜው አስተጓጉሏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0