ጋና የዘር ሐረግ ትስስሯን ለማጠናከር 300 መምህራንን በባሃማስ ልታሰማራ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታወቁ

ሰብስክራይብ

ጋና የዘር ሐረግ ትስስሯን ለማጠናከር 300 መምህራንን በባሃማስ ልታሰማራ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታወቁ

​በአዲሱ የትምህርት ትብብር ስምምነት የመጀመሪያ ምዕራፍ መምህራኑ ወደ ባሃማስ እንደሚጓዙ የጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳም ኦኩዜቶ አብላክዋ የካሪቢያኗ ሀገር 53ኛ ዓመት የነፃነት በዓል ላይ ለመታደም በሄዱበት ወቅት አስታውቀዋል።

ይህ በትምህርት ዘርፍ የተጀመረው ጥረት ከፍተኛ ስኬት ከተመዘገበበት የሕክምና ዘርፍ ትብብር ቀጥሎ የመጣ ነው። ሚኒስትሩ እንዳሉት፣ የባሃማስ ባለስልጣናት በተመሳሳይ ስምምነት መሠረት እያገለገሉ የሚገኙትን የጋና ነርሶች መልካም የስራ ስነ-ምግባር አስቀድመው አሞካሽተዋል።

​ይህ ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጥልቅ የታሪካዊ ዘር ትስስር የሚያጠናክር ሲሆን፣ አክራ ለዜጎቿ ተጨባጭ ጥቅም የሚያስገኝ ተፅዕኖ ፈጣሪ ዲፕሎማሲ ለመከተል ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ሚኒስትሩ አፅንዖት ሰጥተዋል።

ℹ ባሃማስ ከምዕራብ አፍሪካ ጋር ጠንካራ ታሪካዊ ትስስር ያላት ሲሆን፣ በርካታ ባሃማሳውያንም የዘር ሐረጋቸውን አሁን ካለችው ጋና እና ከአጎራባች ቀጣናዎች ጋር ያገናኛሉ።

: በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0