ሩሲያ እና ቱንዚያ ለአፍሪካ መረጋጋት ትብብራቸውን እንደሚያጠናክሩ ላቭሮቭ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopiaሩሲያ እና ቱንዚያ ለአፍሪካ መረጋጋት ትብብራቸውን እንደሚያጠናክሩ ላቭሮቭ ተናገሩ
ሩሲያ እና ቱንዚያ ለአፍሪካ መረጋጋት ትብብራቸውን እንደሚያጠናክሩ ላቭሮቭ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.07.2026
ሰብስክራይብ

ሩሲያ እና ቱንዚያ ለአፍሪካ መረጋጋት ትብብራቸውን እንደሚያጠናክሩ ላቭሮቭ ተናገሩ

​ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሁለቱ ሀገራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት የተመሰረተበትን 70ኛ ዓመት አስመልክተው ለቱንዚያው አቻቸው መሐመድ አሊ ናፍቲ በላኩት የእንኳን አደረሳችሁ የቴሌግራም መልዕክት፣ በአካባቢው ደህንነትንና መረጋጋትን በማስፈን ረገድ ያላቸውን የጋራ ፍላጎት አፅንዖት ሰጥተው ገልጸዋል።

ላቭሮቭ፣ “የሩሲያ እና የቱንዚያ ግንኙነት ለሁለቱ ሀገራት ህዝቦች ጥቅም፣ እንዲሁም በአፍሪካ እና በሜዲትራኒያን ቀጣና መረጋጋትና ደህንነትን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በተሳካ ሁኔታ መጠናከሩን እንደሚቀጥል ሙሉ እምነት አለኝ”  ሲሉ ተናግረዋል።

​በሞስኮ እና በቱንዚያ መካከል ያለው ትስስር በወዳጅነት እና በጋራ መከባበር ላይ የተገነባ ረጅም ታሪክ ያለው መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ በነዚህ አሥርት ዓመታት ውስጥ ሁለቱ ወገኖች በባለብዙ ዘርፍ የሁለትዮሽ ትብብር ላይ ከፍተኛ ልምድ ማካበታቸውንና ይህም በሂደት እያደገ መምጣቱን አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0