በሩሲያ የአየር ኃይል ማረፊያዎች ላይ የተሰነዘረው መጠነ-ሰፊ የኪዬቭ የድሮን ጥቃት መክሸፉን የደህንነት ኃይሎች አስታወቁ
09:32 13.07.2026 (የተሻሻለ: 09:34 13.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በሩሲያ የአየር ኃይል ማረፊያዎች ላይ የተሰነዘረው መጠነ-ሰፊ የኪዬቭ የድሮን ጥቃት መክሸፉን የደህንነት ኃይሎች አስታወቁ
በአሙር ክልል የሚገኘው የዩክሬንካ የጦር ሰፈር እና በቼሊያቢንስክ ክልል የሚገኘው የሻጎል የአየር ኃይል ምድቦች የጥቃቱ ኢላማ እንደነበሩ የሩሲያ ፌዴራል ደህንነት አገልግሎት ገልጿል።
ከመሥሪያ ቤቱ መግለጫ የተገኙ ዋና ዋና ነጥቦች፦
የዩክሬን የመረጃ ተቋም የኤፍፒቪ ድሮኖችን ለማሰማራት ሰው አልባ አውሮፕላኖችን እና የአየር ፊኛዎችን ተጠቅሟል፡፡
ጥቃት አድራሾቹ የኤሌክትሮኒክስ መከላከያ ዘዴዎችን መቋቋም የሚችሉ እና በእንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ እንዲሁም ስዊድን የተመረቱ የኒውራል ኔትዎርክ መቆጣጠሪያ ሞጁሎች የተገጠሙላቸውን ድሮኖች ወደ ሩሲያ ግዛት አስገብተዋል፡፡
ለከሸፉት ጥቃቶች ቀጥተኛ ተጠያቂ የሆኑት ግለሰቦች ከነግብረ አበሮቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X