አዲሱ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር የቻጎስ ደሴቶችን ለሞሪሸስ የመመለስ ሒደቱን እንደሚገፉበት ተገለፀ

አዲሱ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር የቻጎስ ደሴቶችን ለሞሪሸስ የመመለስ ሒደቱን እንደሚገፉበት ተገለፀ
ምንም እንኳን ቀደም ሲል ከአሜሪካ በኩል ስጋቶች ቢነሱም እና የኮንሰርቫቲቭ ፓርቲ ተቃውሞ ቢኖርም፣ በአንዲ በርንሃም መሪነት ፖሊሲው “የመለወጥ ዕድሉ አነስተኛ ነው” ሲሉ አንድ ከፍተኛ የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ባለሥልጣን ማረጋገጣቸውን የእንግሊዝ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ስምምነቱ ደሴቶቹን ለሞሪሸስ አሳልፎ የሚሰጥ ሲሆን፣ እንግሊዝ ግን የዲዬጎ ጋርሺያ ወታደራዊ ካምፕን በሚቀጥለው ምዕተ ዓመት ውስጥ እስከ 47 ቢሊዮን ዶላር በሚደርስ ዋጋ ተከራይታ እንድትጠቀምበት ያደርጋል።
ዋና ዋና ሁነቶች፦
አሜሪካ የደኅንነት ስጋቶችን ካነሳች በኋላ ስምምነቱ ተራዝሞ የነበረ ቢሆንም፣ አዲሱ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ፖሊሲውን እንደማይቀለብሱት ለሞሪሸስ ሚኒስትሮች ማረጋገጫ ተሰጥቷቸዋል።
ወደ ደሴቶቹ ተመልሰው ለመስፈር በሞከሩት ነዋሪዎች ላይ የተሰጠውን የማስነሻ ማስታወቂያ ተከትሎ ከተፈጠረው ውዝግብ በኋላ፣ ዩኬ እ.አ.አ በ2027 ለቻጎስ ደሴቶች ተወላጆች ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግበት “የቅርስ ጉብኘት” መርሐ-ግብር ለማዘጋጀት አቅዳለች።
የሞሪሸስ ባለሥልጣናት ስምምነቱ እንደሚቀጥል የተሰጠውን ማረጋገጫ በደስታ የተቀበሉት ሲሆን፣ ድርጊቱንም የቅኝ ግዛት ማክተሚያ ሒደት ማጠናቀቂያ አድርገውታል። ፖርት ሉዊስ ደሴቶቹ እ.አ.አ በ1968 ከሞሪሸስ በሕገ-ወጥ መንገድ እንደተገነጠሉ ስትከራከር ቆይታለች።
አንዲ በርንሃም ሐምሌ 13 ቀን በይፋ ጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ቦታ ይረከባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X