ሩዋንዳ ዕድሜያቸው 60 እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ዜጎች ልዩ የአረጋውያን የሕክምና አገልግሎት ጀመረች
16:59 12.07.2026 (የተሻሻለ: 17:04 12.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩዋንዳ ዕድሜያቸው 60 እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ዜጎች ልዩ የአረጋውያን የሕክምና አገልግሎት ጀመረች
የጤና ሚኒስትሩ ሳቢን ንሳንዚማና በፓርላማ የጋራ ስብሰባ ላይ እንዳወጁት፣ ይህ ልዩ የአገልግሎት ዓይነት የተጀመረው በሀገሪቱ የሰው ልጅ የዕድሜ ጣሪያ በመጨመሩ እና የአረጋውያን ቁጥር እያደገ በመምጣቱ ነው።
ዋና ዋና ዝርዝሮች፦
🟠 እ.አ.አ በ2030 የዕድሜ ጣሪያ 80 ዓመት ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህም የአረጋውያን ዜጎችን ቁጥር ይጨምረዋል።
🟠 አዲሱ የአረጋውያን ሕክምና አገልግሎት እንደ ሕፃናት ሕክምና ሁሉ ለአረጋውያን ፍላጎት ተስማሚ ተደርጎ የተዘጋጀ ይሆናል።
🟠ሩዋንዳ በአረጋውያን እንክብካቤ ላይ የሰለጠኑ ዶክተሮችን አስቀድማ ያዘጋጀች ሲሆን፣ እነዚህም አገልግሎት መስጠትና ተጨማሪ የጤና ባለሙያዎችን ማሰልጠን ይጀምራሉ።
“ዋናው ነገር ዕድሜ ቁጥር ብቻ እንዲሆን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግና ጤናን መንከባከብ ነው። አንድ ሰው 80 ዓመት ደርሶ፣ የልጅ ልጆቹን አዝሎ፣ አሁንም ከእነሱ ጋር እግር ኳስ መጫወት መቻል አለበት” ብለዋል ንሳንዚማና።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X