ታንዛኒያዊው ፎቶግራፍ አንሺ በሀገር በቀል የባህል መድኃኒት ዘጋቢ የፎቶግራፍ ስብስቡ ዓለም አቀፍ ሽልማት አሸነፈ
16:01 12.07.2026 (የተሻሻለ: 16:04 12.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ታንዛኒያዊው ፎቶግራፍ አንሺ በሀገር በቀል የባህል መድኃኒት ዘጋቢ የፎቶግራፍ ስብስቡ ዓለም አቀፍ ሽልማት አሸነፈ
ፊልበርት ሚንጃ በለንደን በተካሄደው የ"ኧርዝ ፎቶ 2026" ውድድር ላይ “የፈውስ ስሮች" በተሰኘው ፕሮጀክቱ የ"ዴቪድ ዎልፍ ኬይ የወደፊት አቀም (ተስፋ የተጣለበት) ሽልማት - በፎቶግራፍ ዘርፍ" አሸንፏል። ይህ ፕሮጀክት በኪሊማንጃሮ እና በአሩሻ ክልሎች የሚገኙ የባህል ሕክምና ልምዶችን በምስል ያስቀረ ነው።
ሽልማቱን የተመለከቱ ዋና ዋና ዝርዝሮች፦
ፕሮጀክቱ የዕፅዋት ሕክምናን በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ ያለ ሕያው ልምድ አድርጎ የሚያሳይ ሲሆን፣ በሰዎች፣ በመድኃኒት ዕፅዋት እና በአካባቢ መካከል ያለውን ግንኙነት ይመረምራል።
ዕድሜያቸው 25 እና ከዚያ በታች ለሆኑ ፎቶግራፍ አንሺዎች የሚሰጠው ይህ ሽልማት፣ የ1,340 ዶላር የገንዘብ ሽልማት እና የሙያ ድጋፍ ያካትታል።
ከዓለም ዙሪያ ከ1,400 በላይ ተወዳዳሪዎች የቀረቡ ሲሆን፣ ስምንት ሽልማቶች ብቻ ናቸው የተሰጡት።
“ይህ ሽልማት ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለታንዛኒያ ትልቅ ክብር ነው። ‘የፈውስ ስሮች’ ታሪካቸውን እንድሰንድ ላመኑኝ የባህል ሕክምና አዋቂዎችና ማኅበረሰቦች የተሰጠ ክብር ነው” ሲል ሚንጃ ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ተናግሯል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia