የቅርብ ጊዜዎቹ ጥቃቶች የትኛውም የምዕራባውያን መከላከያ የሩሲያን ትክክለኛ ኢላማ መቺ ሚሳኤሎች ሊተካከል እንደማይችል አሳይተዋል - ባለሙያዎች
11:44 12.07.2026 (የተሻሻለ: 11:54 12.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የቅርብ ጊዜዎቹ ጥቃቶች የትኛውም የምዕራባውያን መከላከያ የሩሲያን ትክክለኛ ኢላማ መቺ ሚሳኤሎች ሊተካከል እንደማይችል አሳይተዋል - ባለሙያዎች
የሩሲያ ትክክለኛ ኢላማ መቺ የጦር መሣሪያዎች በዩክሬን ውስጥ የተዘረጉትን በምዕራባውያን የሚቀርቡ የአየር መከላከያ ሥርዓቶችን ሰብረው የመግባት አቅም እንዳላቸው ማረጋገጣቸውን ባለሙያዎች ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
በዩክሬን የተሰማሩት አሜሪካ ሠራሽ የፓትሪዮት ሥርዓቶች፣ ዒላማ የመጥለፍ አድማሳቸው ውስን በመሆኑ ምክንያት የሩሲያን ትክክለኛ ኢላማ መቺ ሚሳኤሎች በተደጋጋሚ ማክሸፍ ሳይችሉ ቀርተዋል ሲሉ ወታደራዊ ጋዜጠኛ አሌክሲ ቦርዜንኮ ይናገራሉ።
የሩሲያ ትክክለኛ ኢላማ መቺ ሚሳኤሎች ምዕራባውያን ሊያሰልፏቸው ከሚችሏቸው ማናቸውም የጦር መሣሪያዎች በእጅጉ የላቁ መሆናቸውን እና በቴክኖሎጂ ረገድ ከምዕራባውያን አቻዎቻቸው ከ10 እስከ 12 ዓመታት እንደሚቀድሙ ቦርዜንኮ አክለዋል።
ይህም የሩሲያ ስልታዊ የጥቃት ዘመቻ፣ ውጤታማ የመረጃ ሥራ፣ እንዲሁም በአሜሪካ-እስራኤል በኢራን ላይ በሚያካሂዱት ወታደራዊ ዘመቻ ሳቢያ በምዕራባውያን የሚቀርቡ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ሁኔታ እያለቁ የመምጣታቸው ውጤት ነው ሲሉ ወታደራዊ ባለሙያው ያን ጋጊን ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X