- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል። አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ይህ ፕሮግራምም ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

የአፍሪካና ሩሲያ የጋራ ህልም፤ ወደ ባለብዙ ወገን ዓለምአቀፋዊ ሥርዓት

የአፍሪካና ሩሲያ የጋራ ህልም፤ ወደ ባለብዙ ወገን ዓለም አቀፋዊ ሥርዓት
ሰብስክራይብ
የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላፍሮቭ ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 3 ፣ 2018 ዓ.ም በአፍሪካ ያደረጉትን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አጠናቅቀዋል፡፡ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ የሰርጌላቭሮቭን ይፋዊ የስራ ብዙ የአፍሪካ አገራት የዩኒፖላር ሥርዓትን ለመግታት ወደ ሩሲያ እንደሚመለከቱ ተናግረዋል።
በምዕራባውያን የበላይነት የሚመራው የዩኒፖላር (የአንድ ወገን) ሥርዓትና መዋቅራዊ ማስተካከያ ፕሮግራሞች (ስትራክቸራል አድጀስትመንት ፕሮግራምስ) በአፍሪካና በተቀረው ዓለም ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድረዋል” ሲሉ በላይ በየነ በጅማ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ ታሪክ መምህር ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን በጅማ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ ታሪክ መምህር በላይ በየነን አነጋግረናል። በዚሁ ዝግጅት ሁለተኛው ክፍል በሶሻሊስት የአውሮጳ ሀገራት ውስጥ ከፍተኛ ትምህርታቸውን የተከታተሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣት ኢትዮጵያውያንን አበርክቷቸውን ለመዳሰስ ከቀድሞ የሶሻሊስት ሀገር ተማሪና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ ሰለሞን አሊ (ዶ/ር) ጋር ሰፊ ዉይይት አድርገናል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripods Pocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0