‘የእውነተኛ ጦር ሰራዊት ምሥረታ’ - የሳኅል ሀገራት ጥምረት የመከላከያ ሚኒስትሮች ለተባበረው ኃይል የተዘጋጀውን የረቂቅ ደንብ ገመገሙ

ሰብስክራይብ

‘የእውነተኛ ጦር ሰራዊት ምሥረታ’ - የሳኅል ሀገራት ጥምረት የመከላከያ ሚኒስትሮች ለተባበረው ኃይል የተዘጋጀውን የረቂቅ ደንብ ገመገሙ

​ የሳኅል ሀገራት ጥምረት የመከላከያ ሚኒስትሮች፣ ጥምረቱ ለሚያደራጀው የተባበረ ኃይል የተዘጋጀውን የረቂቅ ደንብ ለመገምገም በትናንትናው ዕለት በኡጋዱጉ ተገናኝተዋል።

​ ስብሰባውን በሊቀመንበርነት የመሩት የቡርኪና ፋሶ የጦር እና የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ሜጀር ጄኔራል ሴሌስቲን ሲምፖሬ ናቸው።

​ እንደ ሲምፖሬ ገለጻ፣ የዚህ ስብሰባ ዓላማ ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጄር በጋራ ለሚገነቡት "እውነተኛ ጦር ሠራዊት" መሠረት መጣል ነው።

​" ዋናው ፍላጎታችን የሰው ኃይል እና የቁሳቁስ አቅማችንን ማጠናከር እንዲሁም ወታደራዊ ዘመቻዎችን ይበልጥ ማሳደግ ነው" ብለዋል።

ዋና ዋና ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች፦

​ የሰው ኃይል እና ወታደራዊ አቅምን ማጠናከር፤

የትጥቅ እና የሎጅስቲክስ አቅርቦትን ማደራጀት፤

የመስክ ዘመቻዎችን ማጠናከር እና

የጦር ኃይሉ በማንኛውም ጊዜ ዝግጁ ሆኖ መቆየቱን ማረጋገጥ ናቸው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0