‘የእውነተኛ ጦር ሰራዊት ምሥረታ’ - የሳኅል ሀገራት ጥምረት የመከላከያ ሚኒስትሮች ለተባበረው ኃይል የተዘጋጀውን የረቂቅ ደንብ ገመገሙ
18:34 11.07.2026 (የተሻሻለ: 18:44 11.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
‘የእውነተኛ ጦር ሰራዊት ምሥረታ’ - የሳኅል ሀገራት ጥምረት የመከላከያ ሚኒስትሮች ለተባበረው ኃይል የተዘጋጀውን የረቂቅ ደንብ ገመገሙ
የሳኅል ሀገራት ጥምረት የመከላከያ ሚኒስትሮች፣ ጥምረቱ ለሚያደራጀው የተባበረ ኃይል የተዘጋጀውን የረቂቅ ደንብ ለመገምገም በትናንትናው ዕለት በኡጋዱጉ ተገናኝተዋል።
ስብሰባውን በሊቀመንበርነት የመሩት የቡርኪና ፋሶ የጦር እና የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ሜጀር ጄኔራል ሴሌስቲን ሲምፖሬ ናቸው።
እንደ ሲምፖሬ ገለጻ፣ የዚህ ስብሰባ ዓላማ ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጄር በጋራ ለሚገነቡት "እውነተኛ ጦር ሠራዊት" መሠረት መጣል ነው።
" ዋናው ፍላጎታችን የሰው ኃይል እና የቁሳቁስ አቅማችንን ማጠናከር እንዲሁም ወታደራዊ ዘመቻዎችን ይበልጥ ማሳደግ ነው" ብለዋል።
ዋና ዋና ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች፦
የሰው ኃይል እና ወታደራዊ አቅምን ማጠናከር፤
የትጥቅ እና የሎጅስቲክስ አቅርቦትን ማደራጀት፤
የመስክ ዘመቻዎችን ማጠናከር እና
የጦር ኃይሉ በማንኛውም ጊዜ ዝግጁ ሆኖ መቆየቱን ማረጋገጥ ናቸው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X