የምስራቅ አፍሪካ ፌዴሬሽን ለአኅጉራዊ ደህንነት ዋስትና የሚሆን ብቸኛው መንገድ ነው - የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት
17:24 11.07.2026 (የተሻሻለ: 17:34 11.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የምስራቅ አፍሪካ ፌዴሬሽን ለአኅጉራዊ ደህንነት ዋስትና የሚሆን ብቸኛው መንገድ ነው - የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት
ዮዌሪ ሙሴቬኒ የተበታተኑ ሀገራት የረጅም ጊዜ ደህንነትን ማረጋገጥ እንደማይችሉ በማስጠንቀቅ፣ ለአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ውህደት ያቀረቡትን ጥሪ በድጋሚ አድሰዋል።
በደቡብ ምስራቅ ኡጋንዳ በሚገኝ ወታደራዊ ኮሌጅ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት ሙሴቬኒ፣ ዘላቂ ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዋና ዋና ምሰሶዎችን ጠቅሰዋል፦
ዜጎችን በንግድ ኢኮኖሚ (በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ እና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ) ውስጥ በማሳተፍ ድህነትን ማስወገድ፤
እድገትን ለማፋጠን ግንዛቤን ማስፋት፣ የሂሳብ እና የክህሎት ስልጠናዎችን ማሳደግ እና
የባህር ኃይል እና ጠንካራ የአየር ኃይል ለማግኘት የምስራቅ አፍሪካ ፌዴሬሽንን መመስረት፣ እነዚህ ኡጋንዳ በብቸኝነት ልትገነባቸው የማትችላቸው አቅሞች ናቸው።
አሜሪካን፣ ቻይናን፣ ሩሲያን እና ሕንድን በምሳሌነት የጠቀሱት ሙሴቬኒ፣ ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ እና የሕዋ አቅሞችን በተሳካ ሁኔታ ማሳደግ የሚችሉት ትላልቅ እና የተዋሃዱ ሀገራት ብቻ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X