ኢትዮጵያ ለኬንያ 1 ኪሎ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ኃይል በ24 ብር ከ07 ሳንቲም ለማቅረብ ተስማማች

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ ለኬንያ 1 ኪሎ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ኃይል በ24 ብር ከ07 ሳንቲም ለማቅረብ ተስማማች

  ስምምነቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኤሌክትሪክ ንግድ ለማጠናከር፣ በድንበር አካባቢዎች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማስፋፋትና የምስራቅ አፍሪካን የኢነርጂ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጌቱ ገረመው፤ ስምምነቱ “ትስስሯ የተጠናከረ ምስራቅ አፍሪካን እውን ለማድረግ እንደሚያግዝ” ጠቁመው፤ “ኢነርጂ የሀብት ምንጭ ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ሕዝብ ወደ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ እድገት የሚያደርስ ድልድይ ነው” ብለዋል፡፡

የኬንያ ኤሌትሪክ ኃይል ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጆሴፍ ሲሮር በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር አካባቢ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች የስምምነቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ መሆናቸው፤ በሁለቱ ወንድማማች ሕዝቦች መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0