የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በሆቴል እና ማረፊያ አገልግሎቶች ላይ የ5 በመቶ ግብር ጣለ
19:59 10.07.2026 (የተሻሻለ: 20:04 10.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በሆቴል እና ማረፊያ አገልግሎቶች ላይ የ5 በመቶ ግብር ጣለ
መመሪያው ከአንድ እስከ ሰባት ኮከብ ደረጃ ያላቸውን የቅንጦት ሆቴሎች እንዲሁም ደረጃ ያልወጣላቸውን ሆቴሎች፣ ሪዞርቶች፣ ሎጆች፣ ሞቴሎች፣ ፔንሲዮኖች እና የእንግዳ ማረፊያዎችን ይመለከታል።
በደንቡ መሠረት ዕለታዊ የመኝታ አገልግሎት ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ ሳይታከል 5% ታክስ ይቆረጣል።
በተጨማሪም፤ ለምግብ፣ መጠጥ፣ ስፓ እና ሌሎች የግል እንክብካቤ አገልግሎቶች የሚከፈሉ ተጨማሪ ክፍያዎች ከዚህ ታክስ ስሌት ውጪ ናቸው ሲል የሀገር ውስጥ የግል ሚዲያ ነው የዘገበው።
ከአዲሱ የማዘጋጃ ቤት ግብር የሚሰበሰበው ገቢ ለከተማ መሠረተ ልማት ግንባታ፣ ለአዳዲስ የቱሪስት መስህቦች ልማት እንዲሁም ለሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች መሻሻልና መስፋፋት ይውላል ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X