ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኢነርጂ ትስስር ለማፋጠን ቃል በመግባት፤ የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ሊቀመንበርነትን ተረከበች

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኢነርጂ ትስስር ለማፋጠን ቃል በመግባት፤ የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ሊቀመንበርነትን ተረከበች

“ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ለማፋጠን እና የምሥራቅ አፍሪካን በኃይል የተሳሰረ ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያ የመፍጠር ራዕይ ለማሳካት ከአባል ሀገራት ጋር ትብብሯን ለማጠናከር ቁርጠኛ ነች” ሲሉ የኢትዮጵያ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ በአዲስ አበባ በተካሄደው የስብስቡ 22ኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት መድረክ ላይ ተናግረዋል።

 

ሀገሪቱ ግብፅን በመተካት ነው ሊቀመንበርነቱን የጨበጠችው። ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ታንዛንያ፣ ኡጋንዳ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ግብፅ፣ ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ጅቡቲ፣ ሶማሊያና ሊቢያ የትስስሩ 13 አባል ሀገራት ናቸው።

የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር በአባል ሀገራቱ መካከል የጋራ የኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃቀም፣ የኃይል ግብይት እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል የተመሠረተ ነው።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0