ናይጄሪያ ደቡብ ኮሪያን በመቅደም በ2026 በዓለም ከፍተኛ ትርፋማውን የአክሲዮን ገበያ አስመዘገበች
17:41 10.07.2026 (የተሻሻለ: 17:44 10.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ናይጄሪያ ደቡብ ኮሪያን በመቅደም በ2026 በዓለም ከፍተኛ ትርፋማውን የአክሲዮን ገበያ አስመዘገበች
ብሉምበርግ 92 የዓለም የአክሲዮን ገበያዎችን በማነጻጸር ባወጣው መረጃ፤ የናይጄሪያ አክሲዮኖች በዚህ ዓመት እስካሁን በዶላር ሲሰላ የ67 በመቶ ዕድገት በማስመዝገብ፤ የደቡብ ኮሪያን የ66 በመቶ ዕድገት በጠባብ ልዩነት በልጠዋል።
የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን እንደገለጹት የዚህ አስደናቂ ዕድገት አንቀሳቃሾች፦
የፕሬዚዳንት ቲኑቡ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች፣
ጠንካራ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እና የነዳጅ ዋጋ መጨመር፣
የውጭ ሀገር ባለሀብቶች ፍላጎት በድጋሚ ማደጉ፣
የናይጄሪያ ገንዘብ ናይራ በዚህ ዓመት ከዶላር አንጻር የአራት በመቶ ገደማ ጥንካሬ ማሳየቱ።
ዓለም አቀፉ የጠቋሚ መረጃዎች አቅራቢ ኤስ ኤንድ ፒ ዶው ጆንስ ናይጄሪያን ወደ ታዳጊ ገበያ ደረጃ ለማሳደግ እንዳሰበ የተሰማ ሲሆን ይህም ተጨማሪ ተቋማዊ መዋዕለ ንዋይ ሊስብ እንደሚችል ተገልጿል።
በተጨማሪም የገበያ ተዋናዮች የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ ወደ አክሲዮን ገበያ ሊገባ የሚችልበትን ዕድል በጉጉት እየተጠባበቁ ሲሆን ባለሀብቱ አሊኮ ዳንጎቴ የተቋሙን 10 በመቶ ድርሻ በተለያዩ የአፍሪካ አክሲዮን ገበያዎች ለሽያጭ ለማቅረብ አቅደዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X