ብርቅዬው ዋልያ አይቤክስ ቁጥሩ ማሽቆልቆሉን ተከትሎ ለመጥፋት በእጅጉ የተጋለጠ በሚል መደብ ውስጥ በድጋሚ ተካተተ

ሰብስክራይብ

ብርቅዬው ዋልያ አይቤክስ ቁጥሩ ማሽቆልቆሉን ተከትሎ ለመጥፋት በእጅጉ የተጋለጠ በሚል መደብ ውስጥ በድጋሚ ተካተተ

 

በኢትዮጵያ ሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ብቻ የሚገኘው ይህ የዱር እንሰሳ፤ ቀደም ሲል የተደረጉ ቆጠራዎች ቁጥሩ እያገገመ መሆኑን በመጠቆማቸው "ተጋላጭ" በሚል መደብ ስር ቆይቶ ነበር።

 

ሆኖም በታህሳስ 2017 የተከናወነ ምልከታ የዱር እንስሳው በ2016 ተካሂዶ ከነበረው ቆጠራ በ18 ቀንሶ 271 እንደደረሰ አመልክቷል።

ለዝርያው መመናመን በምክንያትነት የተጠቀሱ ጉዳዮች፦

 

ሕገ-ወጥ አደን፣

የተፈጥሮ መኖሪያ መራቆት፣

እየጨመረ የመጣ የሰዎች ድንበር መተላለፍ ።

 

ባለፉት አራት አስርት ዓመታት የዋልያ አይቤክስ የጥበቃ ደረጃ በተደጋጋሚ መለዋወጡን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0