- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ከአሰላለፍ ነፃነት ወደ ስትራቴጂካዊ ሉዓላዊነት፦ የአፍሪካ አዲሱ የውጭ ፖሊሲ አካሄድ

ከአሰላለፍ ነፃነት ወደ ስትራቴጂካዊ ሉዓላዊነት፦ የአፍሪካ አዲሱ የውጭ ፖሊሲ አካሄድ
ሰብስክራይብ
"አፍሪካውያን በዓለም አቀፍ ግንኙነት ውስጥ ሁለቱንም ወገን ተጠቃሚ የሚያደርግ አካሄድን ሲያስቡ፤ የትኛውንም ሀገር ውይም ቀጠና በፍፁም በዕውር ድንብር ማመን የለባቸውም። በመጀመሪያ ደረጃ አፍሪካውያን ማድረግ ያለባቸው ትልቁ ነገር በመካከላቸው እምነትን መገንባት ነው።" ሲሉ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ዳዊት መዝገበ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ የአፍሪካ አገራት ጉብኝታቸውን ሐምሌ 30 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ጀምረው ነሐሴ 1 በኒጀር እና ነሐሴ 2 ፣ 2018 ዓ.ም ሞዛምቢክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ነው፡፡ ይህ በአህጉሪቱ ላይ ምን አዲስ የፖለቲካ አንድምታ ይዟል? ከቀዝቃዛው ጦርነት ዘመን የ"አሰላለፍ ነፃነት" (non-alignment) መርህ ወጥታ፣ አፍሪካ ዛሬ ወደምትከተለው ስትራቴጂካዊ ሉዓላዊነት እያደረገችው ያለው ሽግግር በተግባር ምን ማለት ነው?
በዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ከሆኑት ዳዊት መዝገበ (ዶ/ር) ጋር በመሆን፣ ተለዋዋጩን የአለም የኃይል ሚዛን እና የአፍሪካን አዲስ የዲፕሎማሲ በጥልቀት እንመረምራለን።
ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0