ሮሳቶም በግብጹ የኤል ዳባ የኒውክሌር ኃይል ጣቢያ የሁለተኛውን የኃይል ማመንጫ ክፍል ተከላ ጀመረ

ሰብስክራይብ

ሮሳቶም በግብጹ የኤል ዳባ የኒውክሌር ኃይል ጣቢያ የሁለተኛውን የኃይል ማመንጫ ክፍል ተከላ ጀመረ

በሥነ-ሥርዓቱ የግብጽ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞስጠፋ ማድቡሊ፣ የሮሳቶም ዋና ዳይሬክተር አሌክሲ ሊካቾቭ እና የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ ኃላፊ ራፋኤል ግሮሲ መገኘታቸውን የስፑትኒክ ባልደረባ ዘግቧል።

🟡 ስለ ፕሮጀክቱ፦

የገንዘብ ምንጭ (ፋይናንስ)፦ ጣቢያው የሚገነባው በ25 ቢሊዮን ዶላር የሩሲያ ብድር ድጋፍ ነው።

ሪአክተሮች፦ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 1,200 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አራት የሦስተኛ ትውልድ ቪቪኢአር-1200 ሪአክተሮች ይኖሩታል።

የሮሳቶም ኃላፊነቶች፦

የጣቢያው ግንባታ፣

የኒውክሌር ነዳጅ አቅርቦት፣

የሀገር ውስጥ ባለሙያዎችን ማሠልጠን፣

ጣቢያው ሥራ ከጀመረ በኋላ ለመጀመሪያዎቹ 10 ዓመታት የማንቀሳቀስ እና የጥገና ሥራዎችን ማከናወን።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0