የኢቦላ ወረርሽኝ ወቅታዊ መረጃዎች፦ የመካከለኛው እና ምሥራቅ አፍሪካ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ሪፖርት
17:33 09.07.2026 (የተሻሻለ: 17:34 09.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢቦላ ወረርሽኝ ወቅታዊ መረጃዎች፦ የመካከለኛው እና ምሥራቅ አፍሪካ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ሪፖርት
ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ - የኮሙዩኒኬሽን እና ሚዲያ ሚኒስቴር 1,759 ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን አረጋግጧል፦
▪ 600 ሞት፣
▪ 750 ያገገሙ፣
▪ 34 በመቶ የሞት ምጣኔ፣
▪ በወረርሽኙ የተጠቁ ግዛቶች፦ ኢቱሪ፣ ሰሜን ኪቩ፣ ደቡብ ኪቩ፣ ሾፖ፡፡
ኡጋንዳ - የጤና ሚኒስቴር 20 ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን አረጋግጧል፦
▪ 2 ሞት፣
▪ 17 ያገገሙ
▪ 1 በሆስፒታል በሕክምና ላይ ያለ፡፡
ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ - የኢቦላ ወረርሽኝ መዛመትን ለመከላከል የሕክምና ቡድኖች ከኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጋር በሚያዋስነው ድንበር ላይ ተሰማርተዋል።
ቪዲዮ፦ በዲአርሲ ቡኒያ የኢቦላ ተጠቂ መገኘቱን ተከትሎ፤ የንጽሕና ቡድኖች በአንድ ሆቴል የፀረ-በሽታ ኬሚካል መርጨት እና ማፅዳት ሥራ ሲያከናውኑ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X