የግብፅ አሰልጣኝ የታቀደ ሙስና ተፈጽሞብናል በማለት በዓለም ዋንጫው በአርጀንቲና የደረሰባቸውን ሽንፈት ኮነኑ

© telegram sputnik_ethiopiaየግብፅ አሰልጣኝ የታቀደ ሙስና ተፈጽሞብናል በማለት በዓለም ዋንጫው በአርጀንቲና የደሰባቸውን ሽንፈት ኮነኑ
የግብፅ አሰልጣኝ የታቀደ ሙስና ተፈጽሞብናል በማለት በዓለም ዋንጫው በአርጀንቲና የደሰባቸውን ሽንፈት ኮነኑ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.07.2026
ሰብስክራይብ
የግብፅ አሰልጣኝ የታቀደ ሙስና ተፈጽሞብናል በማለት በዓለም ዋንጫው በአርጀንቲና የደረሰባቸውን ሽንፈት ኮነኑ

የግብፅ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆሳም ሀሰን ቁጣ መነሻ በጨዋታው 58ኛ ደቂቃ የቡድኑ አማካይ ሞስጠፋ ዚኮ ያስቆጠራት ግብ በቪዲዮ ረዳት ዳኛ (ቫር) መሰረዙ ነው። ዳኛው ጎሉ ከመቆጠሩ በፊት ማርዋን አቲያ ጥፋት ሰርቷል በሚል ውሳኔውን ያስተላለፉ ሲሆን በጭማሪ ሰዓት ላይ ከግብፅ የአሰልጣኞች ቡድን አባላት አንዱ ቀይ ካርድ ተመልክቷል።


"የተፈጸመው ከስርዓት ውጪ የሆነ የፍትሕ መጓደል ነው። እኛ ደግሞ ምንም ማድረግ አንችልም፤ ምክንያቱም የአፍሪካ እና የእስያ ቡድኖች ምንም ዓይነት ኃይልም ሆነ ተጽዕኖ ያላቸው አይመስልም" ሲሉ ሀሰን ምሬታቸውን ገልጸዋል።


የግብፅ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሃኒ አቡ ሪዳ፤ ለዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማኅበር ይፋዊ የቅሬታ ደብዳቤ ማስገባታቸውን አረጋግጠዋል።

በአትላንታ የተደረገው ጨዋታ ግብፅ እስከ 79ኛው ደቂቃ ድረስ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ከመራች በኋላ በመጨረሻ በአርጀንቲና 3 ለ 2 አሸናፊነት ተጠናቋል።

ውጤቱን ተከትሎ አርጀንቲና በሩብ ፍጻሜው ከስዊዘርላንድ ጋር ትገናኛለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0