በአዲስ አበባ 9.4 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርኃ-ግብር ተጀመረ

© telegram sputnik_ethiopiaበአዲስ አበባ 9
በአዲስ አበባ 9 - Sputnik አፍሪካ, 1920, 07.07.2026
ሰብስክራይብ

በአዲስ አበባ 9.4 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርኃ-ግብር ተጀመረ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ3 ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ከ2 ሚሊዮን በላይ በጎ ፈቃደኞችን የሚያሳትፍ እና እስከ ጥቅምት 2019 ዓ.ም የሚቆይ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርኃ-ግብር በይፋ አስጀምሯል።

🟠በከተማዋ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን አማካኝነት “በጎ ፈቃደኝነት ለአዲስ አበባ ዕድገት” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ይህ ዘመቻ፦

ነፃ ሕክምና፦ ለ110 ሺህ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ነዋሪዎች ነፃ የሕክምና አገልግሎት መስጠት፣

ደም ልገሳ፦ 25 ሺህ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ የሚያስችል ንቅናቄ ማደራጀት፣

ማኅበራዊ ድጋፎች፦ ማዕድ ማጋራት፣ የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች የመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የችግኝ ተከላ እና የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት መስጠትን ያካትታል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0