በአዲስ አበባ 9.4 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርኃ-ግብር ተጀመረ
18:11 07.07.2026 (የተሻሻለ: 18:14 07.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በአዲስ አበባ 9.4 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርኃ-ግብር ተጀመረ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ3 ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ከ2 ሚሊዮን በላይ በጎ ፈቃደኞችን የሚያሳትፍ እና እስከ ጥቅምት 2019 ዓ.ም የሚቆይ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርኃ-ግብር በይፋ አስጀምሯል።
🟠በከተማዋ የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን አማካኝነት “በጎ ፈቃደኝነት ለአዲስ አበባ ዕድገት” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ይህ ዘመቻ፦
▪ ነፃ ሕክምና፦ ለ110 ሺህ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ነዋሪዎች ነፃ የሕክምና አገልግሎት መስጠት፣
▪ ደም ልገሳ፦ 25 ሺህ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ የሚያስችል ንቅናቄ ማደራጀት፣
▪ ማኅበራዊ ድጋፎች፦ ማዕድ ማጋራት፣ የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች የመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የችግኝ ተከላ እና የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት መስጠትን ያካትታል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X