አልጄሪያ የነፃነት ቀኗን እያከበረች ነው

ሰብስክራይብ

አልጄሪያ የነፃነት ቀኗን እያከበረች ነው

አልጄሪያ ስምንት ዓመታትን ከፈጀ ጦርነት በኋላ ከፈረንሳይ የቅኝ ግዛት አገዛዝ ነፃ የወጣች ሲሆን፤ ይህም እ.ኤ.አ. ሐምሌ 1 ቀን 1962 በተካሄደው የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ሕዝበ ውሳኔ ይፋዊ ዕውቅና አግኝቷል።

በጦርነቱ የደረሰው የሕይወት መጥፋት ከ350,000 እስከ 500,000 እንደሚደርስ ቢገመትም፤ የአልጄሪያ ባለሥልጣናት ግን ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ ሞቶችን ጨምሮ የሟቾች ቁጥር እስከ 1.5 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል ይናገራሉ።

“የአሸናፊዋ አልጄሪያ የጀርባ አጥንት የሆነው ሕዝባችን፤ ለውጡን ለማስቀጠል እንዲሁም ዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ ልማትን ለማጠናከር ቆራጥ መሆኑ ሙሉ እምነት አለኝ” ሲሉ ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ተቡን ቅዳሜ ዕለት ለመላ ሀገሪቱ ባደረጉት ንግግር ገልጸዋል።

ዛሬ ሐምሌ 5 (እ.አ.አ.) በመላው ሀገሪቱ ብሔራዊ የዕረፍት ቀን ሲሆን፤ ቀኑን ሙሉ እና በምሽት የፕሬዝዳንት መታሰቢያዎች፣ ወታደራዊ ሰልፎች እና የርችት ትዕይንቶችን ጨምሮ የተለያዩ የበዓል ዝግጅቶች ይከናወናሉ።

ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ ቪዲዮዎች

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0