አዲስ ነፃ የወጡት ግዛቶች የሩሲያን የማጥቃት ጥንካሬ ያሳያሉ - ብራዚላዊ ተንታኝ
13:09 05.07.2026 (የተሻሻለ: 13:14 05.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አዲስ ነፃ የወጡት ግዛቶች የሩሲያን የማጥቃት ጥንካሬ ያሳያሉ - ብራዚላዊ ተንታኝ
የሩሲያ ኃይሎች የዩክሬን እግረኛ ጦር ብርጌዶችን መዳከም በመጠቀም፤ የውጊያ መስመሩን ከዶንባስ ቀጣና ባለፈ እያስፋፉት መሆኑን የ‘ቬልሆ ጄኔራል’ ዋና አዘጋጅ አልበርት ካባሌ ማሪሞን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
ዩክሬን ያላትን ውስን የአየር መከላከያ ሀብቶች እንድታሟጥጥ ጫና እየተደረገባት መሆኑን የገለጹት ማሪሞን፤ ይህም የአየር ክልል ቁጥጥርን ለማስቀጠል ሲባል ምዕራባውያን አዳዲስ ሥርዓቶችን በፍጥነት እንዲያቀርቡ እያስገደዳቸው ነው ብለዋል።
ሞስኮ ኪዬቭን እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እየከተተቻት መሆኑን የገለጹት ተንታኙ፤ ይህም የዩክሬንን የመቋቋም አቅምም ሆነ የአጋሮቿን የገንዘብ ድጋፍ የመቀጠል ፍላጎት የሚፈትን ነው ሲሉ አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X